አንድ የደጋ አጋዘን በ15 ሺህ ዶላር እየታደነ ነው
አንድ የደጋ አጋዘን በ15 ሺህ ዶላር እየታደነ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦና ያዴሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ ደንን ማዕከል ያደረገ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በስፋት ይሰራል፡፡
በዚህም ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት የነበረው አሰራር ደኖችን ለመጠበቅ ህዝብን ያሳተፈ አልነበረም ያሉት አቶ ቦና፤ ይህን አሰራር በመቀየር ህብረተሰቡ እንዲደራጅ በማድረግ ደኖችን እንዲከልልና በውስጡ ያሉ ሃብቶች እንዲጠብቅ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘን ለውጪ ሀገር ዜጎች ለሕጋዊ አደን በማቅረብ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከፍ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
የደጋ አጋዘን በአርሲ እና ባሌ ተራራማ ስፍራዎች እንዲሁም በምዕራብ ሀረርጌ በስፋት የሚገኝ ነው ብለው፤ የውጪ ሀገር ዜጎችም ለስፖርታዊ አደን የሚመርጡት ብርቅዬ እንስሳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ በአዳባ እና ዶዶላ አካባቢዎች ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ለውጪ ዜጎች የደጋ አጋዘንን ለአደንነት እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አደኑን የሚያደርጉት የውጪ ዜጎች ፈቃድ የሚሰጣቸው ሲሆን፤ በአካባቢው ከተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ጋር በመሆን ያረጀ ወንድ የደጋ አጋዘን ተመርጦ እንዲያድኑ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
ማንኛውንም የደጋ አጋዘን ማደን ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑንም አክለዋል፡፡
አንድ የውጪ ዜጎች ለአንድ አጋዘን ለማደን 15 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይከፍላል ያሉት አቶ ቦና፤ አዳኙ ያደነውን የደጋ አጋዘን ከአንገት በላይ ያለው አካል ይዞ መሄድ ይችላል ብለዋል፡፡
ከአደኑ የሚገኘው ገቢ 70 በመቶ የሚሆነው ለኢንተርፕራዞች የሚገባ መሆኑና 30 በመቶውን መንግስት እንደሚወሰድም ተናግረዋል፡፡
Gazette Plus
አንድ የደጋ አጋዘን በ15 ሺህ ዶላር እየታደነ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦና ያዴሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ ደንን ማዕከል ያደረገ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በስፋት ይሰራል፡፡
በዚህም ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት የነበረው አሰራር ደኖችን ለመጠበቅ ህዝብን ያሳተፈ አልነበረም ያሉት አቶ ቦና፤ ይህን አሰራር በመቀየር ህብረተሰቡ እንዲደራጅ በማድረግ ደኖችን እንዲከልልና በውስጡ ያሉ ሃብቶች እንዲጠብቅ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘን ለውጪ ሀገር ዜጎች ለሕጋዊ አደን በማቅረብ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከፍ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
የደጋ አጋዘን በአርሲ እና ባሌ ተራራማ ስፍራዎች እንዲሁም በምዕራብ ሀረርጌ በስፋት የሚገኝ ነው ብለው፤ የውጪ ሀገር ዜጎችም ለስፖርታዊ አደን የሚመርጡት ብርቅዬ እንስሳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ በአዳባ እና ዶዶላ አካባቢዎች ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ለውጪ ዜጎች የደጋ አጋዘንን ለአደንነት እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አደኑን የሚያደርጉት የውጪ ዜጎች ፈቃድ የሚሰጣቸው ሲሆን፤ በአካባቢው ከተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ጋር በመሆን ያረጀ ወንድ የደጋ አጋዘን ተመርጦ እንዲያድኑ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
ማንኛውንም የደጋ አጋዘን ማደን ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑንም አክለዋል፡፡
አንድ የውጪ ዜጎች ለአንድ አጋዘን ለማደን 15 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይከፍላል ያሉት አቶ ቦና፤ አዳኙ ያደነውን የደጋ አጋዘን ከአንገት በላይ ያለው አካል ይዞ መሄድ ይችላል ብለዋል፡፡
ከአደኑ የሚገኘው ገቢ 70 በመቶ የሚሆነው ለኢንተርፕራዞች የሚገባ መሆኑና 30 በመቶውን መንግስት እንደሚወሰድም ተናግረዋል፡፡
Gazette Plus
11 months ago