ስፖርት ለአሸናፊ አገር በሚል መሪ ሀሳብ 21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሄደ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ስፖርት ለአሸናፊ አገር" በሚል መሪ ሀሳብ 21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ተካሄደ።
በመድረኩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ እንዲሁም የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ሸዊት ሻንካን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል ና የክልል የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ የስፖርት አመራሮች እና ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ የኢትዮጵያን የስፖርት ታሪካዊ ሂደቶች የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ አውደርዕይ ለእይታ የሚቀርብ ሲሆን አራት የመወያያ ሀሳቦችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የፓናል ውይይቱም አሸናፊ ብሄራዊ ቡድንን እንዴት እንገንባ፣ የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ይመስላል፣ አሸናፊ ቡድን ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለህዝቦች አንድነት ያለው ሚና እንዲሁም አሸናፊ ቡድንን በመገንባት ረገድ ያሉ ስብራቶችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ነው።
ለሀገራችን ስፖርት ብሎም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ውይይት የመሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ሲሆኑ የመወያያ ሀሳብ የሚያቀርቡት ደግሞ የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ናቸው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ
አሸናፊ ቡድን ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለህዝቦች አንድነት ያለው ሚና በሚል ርዕስ ጹሁፍ አቅርበዋል።
ስፖርት ለሀገር መንግስት ግንባታ ያለውን መወጣት እንዲችል በስርዓት ሊመራ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሚዲያው ሞያዊ ስነምግባርን በጠበቀና ለውጤት በሚጋብዝ ሁኔታ ስፖርታዊ ትችቶችን ሊያቀርቡ ይገባል ብለዋል።
ስፖርት ሰላማዊ ሲሆን ባለሀብቶችን የመሳብ ያለው በመሆኑ ፌድሬሽኖች ባለሀብቶችን በዘርፉ ለማሳተፍ መስራት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ገልጸዋል።
በስፖርት ዘርፉ የሚታዮ ችግሮች የወረስናቸው ችግሮች በመሆናቸው ችግሩን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ ጠቁመዋል።
የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ አሸናፊ ቡድንን በመገንባት ረገድ ያሉ ስብራቶችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ጹሁፍ አቅርበዋል።
የመልካም አስተዳደር እጦት በስፖርት ዘርፍ ውጤት እንዳይመጣ ማድረጉን ገልጸዋል።
ለዚህም አሸናፊ ቡድን ለመገንባት ከስፖርቱ ጋር የተገናኙ ፖሊሲዎች በትክክል ተግባር ላይ እንዲውል መስራት ይገባል ብለዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ የስፖርት ስብራቶችን ለማከም ምን እየተሰራ ነው በሚል የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
ሚኒስትር ዲኤታው እንደገለፁት፣ ስፖርት ለሀገር ያለውን አበርክቶ ሰፋ አድርገን ማየት ስብራቱን ለመጠገን አየነተኛ መፍትሄ ነው።
የመጀመሪያው የስፖርቱ ስብራት ችግር የሲስተም ችግር ነው ያሉት ሚኒስትር ዲኤታው፣ በተለይ ደሞ የአገልግሎት አሰጣጡ ፣ የቅንጅት ችግር እንዲሁም የአካዳሚዎች የስልጠና ማእከላት በበቂ አቅም አለመሆን ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
እነዚህን ስብራቶች ለማከም ምን እየተሰራ ነው ለሚለው በመጀመሪያ የገጠመውን የእይታ ችግር ለመፍታት ሰፊ ስራ በመስራት ከለውጡ ወዲህ ትልቅ ለውጥ እንዳለ፣ስፖርቱን የልማት መሳሪያ ለማድረግ ሰፊ ጥረት እየተደረገ እንደሆኑ ፣ገቢን ለማሳደግ ፣የተለያዩ ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሆነ እና ከፖሊሲ ጋር የተያያዙ ስብራቶችን ለመጠገን ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።
በውይይቱም ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተጋበዙ የስፖርት ቤተሰቦች ተሳታፊ ሆነዋል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ስፖርት ለአሸናፊ አገር" በሚል መሪ ሀሳብ 21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ተካሄደ።
በመድረኩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ እንዲሁም የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ሸዊት ሻንካን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል ና የክልል የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ የስፖርት አመራሮች እና ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ የኢትዮጵያን የስፖርት ታሪካዊ ሂደቶች የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ አውደርዕይ ለእይታ የሚቀርብ ሲሆን አራት የመወያያ ሀሳቦችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የፓናል ውይይቱም አሸናፊ ብሄራዊ ቡድንን እንዴት እንገንባ፣ የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ይመስላል፣ አሸናፊ ቡድን ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለህዝቦች አንድነት ያለው ሚና እንዲሁም አሸናፊ ቡድንን በመገንባት ረገድ ያሉ ስብራቶችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ነው።
ለሀገራችን ስፖርት ብሎም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ውይይት የመሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ሲሆኑ የመወያያ ሀሳብ የሚያቀርቡት ደግሞ የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ናቸው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ
አሸናፊ ቡድን ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለህዝቦች አንድነት ያለው ሚና በሚል ርዕስ ጹሁፍ አቅርበዋል።
ስፖርት ለሀገር መንግስት ግንባታ ያለውን መወጣት እንዲችል በስርዓት ሊመራ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሚዲያው ሞያዊ ስነምግባርን በጠበቀና ለውጤት በሚጋብዝ ሁኔታ ስፖርታዊ ትችቶችን ሊያቀርቡ ይገባል ብለዋል።
ስፖርት ሰላማዊ ሲሆን ባለሀብቶችን የመሳብ ያለው በመሆኑ ፌድሬሽኖች ባለሀብቶችን በዘርፉ ለማሳተፍ መስራት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ገልጸዋል።
በስፖርት ዘርፉ የሚታዮ ችግሮች የወረስናቸው ችግሮች በመሆናቸው ችግሩን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ ጠቁመዋል።
የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ አሸናፊ ቡድንን በመገንባት ረገድ ያሉ ስብራቶችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ጹሁፍ አቅርበዋል።
የመልካም አስተዳደር እጦት በስፖርት ዘርፍ ውጤት እንዳይመጣ ማድረጉን ገልጸዋል።
ለዚህም አሸናፊ ቡድን ለመገንባት ከስፖርቱ ጋር የተገናኙ ፖሊሲዎች በትክክል ተግባር ላይ እንዲውል መስራት ይገባል ብለዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ የስፖርት ስብራቶችን ለማከም ምን እየተሰራ ነው በሚል የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
ሚኒስትር ዲኤታው እንደገለፁት፣ ስፖርት ለሀገር ያለውን አበርክቶ ሰፋ አድርገን ማየት ስብራቱን ለመጠገን አየነተኛ መፍትሄ ነው።
የመጀመሪያው የስፖርቱ ስብራት ችግር የሲስተም ችግር ነው ያሉት ሚኒስትር ዲኤታው፣ በተለይ ደሞ የአገልግሎት አሰጣጡ ፣ የቅንጅት ችግር እንዲሁም የአካዳሚዎች የስልጠና ማእከላት በበቂ አቅም አለመሆን ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
እነዚህን ስብራቶች ለማከም ምን እየተሰራ ነው ለሚለው በመጀመሪያ የገጠመውን የእይታ ችግር ለመፍታት ሰፊ ስራ በመስራት ከለውጡ ወዲህ ትልቅ ለውጥ እንዳለ፣ስፖርቱን የልማት መሳሪያ ለማድረግ ሰፊ ጥረት እየተደረገ እንደሆኑ ፣ገቢን ለማሳደግ ፣የተለያዩ ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሆነ እና ከፖሊሲ ጋር የተያያዙ ስብራቶችን ለመጠገን ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።
በውይይቱም ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተጋበዙ የስፖርት ቤተሰቦች ተሳታፊ ሆነዋል።
11 months ago