Logo
Zehabesha
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ በሚገኘው የሜሪላንድ ግዛት ውስጥ፣ በ13 ዓመት ታዳጊ እየተነዳ በነበረ የተሰረቀ መኪና እና በሌላ ተሽከርካሪ መካከል በደረሰ ከባድ ግጭት የ58 ዓመት አዛውንት ህይወት ማለፉን የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

አደጋው ነሐሴ 4 ቀን 2026 እኩለ ሌሊት አልፎ ንጋት ላይ በጀርማንታውን አካባቢ የተከሰተ ሲሆን፣ በቦታው የደረሱ የድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች ኋይት 2015 ኪያ ኦፕቲማ እና 2007 ዮዮታ ማትሪክስ የተባሉትን ሁለቱን ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ ውድመት ደርሶባቸው አግኝተዋቸዋል። በአደጋው የቶዮታ መኪና አሽከርካሪ የነበረው እና የቨርጂኒያ ግዛት ነዋሪ ዊሊያም ቫንስ ፓይን ዳግማዊ በቦታው ላይ ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።

ፖሊስ ባደረገው ማጣራት ከተከሰቱት ሰዓታት በፊት ተሰርቆ የነበረው የኪያ መኪና ውስጥ ዕድሜያቸው ከ12 እስከ 15 ዓመት የሆኑ ሰባት ህጻናት ተሳፍረው እንደነበር ተገልጿል። መኪናውን እየነዳ የነበረው የ13 ዓመት ወንድ ታዳጊ ሲሆን፣ አደጋውን ተከትሎ በከባድ የጉዳት ሁኔታ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል። ሌሎች በጉዞው ላይ የነበሩት ህጻናትም ወደ አካባቢው የድንገተኛ ህክምና ማዕከላት መዘዋወራቸውን የፖሊስ ተናጋሪዎች አረጋግጠዋል።

ህይወቱ ያለፈው ዊሊያም ቫንስ ፓይን የብሔራዊ የደረጃዎች እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (NIST) የሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ባለሙያ እና የአምስት ልጆች አባት ሲሆን፣ አደጋው የደረሰው ወደ ስራ በመጓዝ ላይ በነበረበት ወቅት ነው። የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ መምሪያ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ምርመራ መጀመሩን ገልጾ፣ የወላጆችን ክትትል እና የልጆችን ደህንነት በተመለከተ አሳሳቢ መሆኑን አመልክቷል።

መኪና ያላችሁ ወላጆች ጥንቃቄ አድርጉ!

1 day ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.