Logo
Getu Temesgen
ግብፅ ሰሞኑን ከፈትኩት ያለችው ማዕከል ምንድን ነው?
#ethiopia | ​ግብፅ ከካይሮ በስተምስራቅ በሚገኘው አዲሱ አስተዳደራዊ ዋና ከተማዋ “ኦክታጎን” በመባል የሚታወቀውን የመንግስት ስትራቴጂካዊ ዕዝ ዋና መሥሪያ ቤት በይፋ ከፍታለች።

ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ይፋዊውን ቻርተር በመፈረም እና የጦር ኃይሎችን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ በማድረግ ተቋሙን መርቀው ከፍተዋል።

​ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ውስብስብ ግቢ እጅግ የረቀቁ የዕዝ፣ የቁጥጥር፣ የኮሙኒኬሽን እና የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶች የተገጠሙለት ነው።

በማዕከላዊ መዋቅር ዙሪያ የተገነቡ 13 ቀጠናዎችን የያዘው ይህ ስብስብ የአፍሪካን አጠቃላይ የወቲደር አቅም ከፍ ያደረገ ነው ተብሏል።

ይህ ፕሮጀክት ግብፅ የጦር ኃይሏን በዘመናዊ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ለማዘመን እና ብሔራዊ ደኅንነቷን ይበልጥ ለማጠናከር የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ጥረት በግልጽ ያሳያል ነው የተባለው።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

1 month ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.