የዓለም ዋንጫ ማሸነፍ የቻሉ ሀገራት…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከፈረንጆቹ 1930 ጀምሮ መደረግ በጀመረው በዓለም ዋንጫ ውድድር ስምንት ሀገራት ብቻ ዋንጫውን ማሳካት ችለዋል፡፡
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብራዚል አምስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን÷ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫውን ያሳካችው በፈረንጆቹ 1958 ነበር፡፡
ከዚያ በመቀጠል በፈረንጆቹ 1962 ሻምፒዮን በመሆን በተከታታይ ዋንጫውን አሳክታለች፡፡
እንዲሁም በ1970፣ 1994 እና 2002 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አምስት ጊዜ ዋንጫውን በማሳካት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡
ከብራዚል በመቀጠል የዓለም ዋንጫን ብዙ ጊዜ ማሳካት የቻሉት ጀርመን እና ጣሊያን ናቸው፡፡
ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች በተመሳሳይ አራት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ጣሊያን በፈረንጆቹ 1934 ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን ስትሆን÷ በድጋሚ በ1938 ዋንጫውን በማሳካት በተከታታይ ሻምፒዮን ለመሆን በቅታለች፡፡
እንዲሁም በፈረንጆቹ 1982 ለሦስተኛ ጊዜ ያሸነፈች ሲሆን÷ ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫውን ያሳካችው በፈረንጆቹ 2006 ነበር፡፡
የአራት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ሀገር ጣሊያን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨምሮ ለተከታታይ ሦስተኛ ጊዜ ከውድድሩ ውጪ የሆነች ሲሆን÷ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችው በፈረንጆቹ 2014 ነበር፡፡
ከዚያ በኋላ ማጣሪያውን ማለፍ ባለመቻሏ ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ ከመድረኩ ውጪ ሆናለች፡፡
ሌላኛዋ አራት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያሸነፈችው ሀገር ጀርመን ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን የሆነችው በ1954 ነበር፡፡
ከዚያ በኋላ በፈረንጆቹ 1974፣ 1990 እና 2014 ላይ በመድረኩ ሻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል፡፡
የደቡብ አሜሪካዋ ሀገር አርጀንቲና ደግሞ ሦስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት ችላለች፡፡
አርጀንቲና ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻለችው በፈረንጆቹ 1978 እንደነበር ይታወሳል፡፡
በፈረንጆቹ 1986 ለሁለተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆነች በኋላ ከ36 ዓመታት ጥበቃ በኋላ በ2022 ለ3ኛ ጊዜ ማሸነፏ ይታወሳል፡፡
ፈረንሳይ እና ዩራጋይ ደግሞ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻሉ ብሔራዊ ቡድኖች ናቸው፡፡
ዩራጋይ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ውድድር ያሸነፈች ሲሆን÷ ወቅቱም በፈረንጆቹ 1930 ነበር፡፡
የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ውድድር ያሸነፈችው ዩራጋይ በወቅቱ ውድድሩን ያዘጋጀችው ራሷ እንደነበረች ይታወሳል፡፡
ዩራጋይ ከዚያ በኋላ በፈረንጆቹ 1950 በድጋሚ ዋንጫውን ማንሳቷ አይዘነጋም፡፡
ፈረንሳይ በፈረንጆቹ 1998 እና 2018 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ ሁለት ጊዜ ከዋንጫው ጋር ተገናኝታለች፡፡
እንግሊዝ እና ስፔን ደግሞ በተመሳሳይ አንድ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
እንግሊዝ በፈረንጆቹ 1966 ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን ያሳካች ሲሆን÷ በወቅቱም የውድድሩ አዘጋጅ ሀገር ራሷ ነበረች፡፡
ከዚያ በኋላ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በመድረኩ ሻምፒዮን መሆን አልቻለም፡፡
ስፔን በፈረንጆቹ 2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪኳ ሻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል፡፡
የፊታችን ሐሙስ በሚጀምረው የ2026 ዓለም ዋንጫ አዲስ ሀገር ሻምፒዮን ይሆናል ወይስ ከዚህ ቀደም ካነሱ ሀገራት መካከል አንዱ ሻምፒዮን ይሆናል የሚለው ይጠበቃል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከፈረንጆቹ 1930 ጀምሮ መደረግ በጀመረው በዓለም ዋንጫ ውድድር ስምንት ሀገራት ብቻ ዋንጫውን ማሳካት ችለዋል፡፡
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብራዚል አምስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን÷ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫውን ያሳካችው በፈረንጆቹ 1958 ነበር፡፡
ከዚያ በመቀጠል በፈረንጆቹ 1962 ሻምፒዮን በመሆን በተከታታይ ዋንጫውን አሳክታለች፡፡
እንዲሁም በ1970፣ 1994 እና 2002 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አምስት ጊዜ ዋንጫውን በማሳካት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡
ከብራዚል በመቀጠል የዓለም ዋንጫን ብዙ ጊዜ ማሳካት የቻሉት ጀርመን እና ጣሊያን ናቸው፡፡
ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች በተመሳሳይ አራት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ጣሊያን በፈረንጆቹ 1934 ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን ስትሆን÷ በድጋሚ በ1938 ዋንጫውን በማሳካት በተከታታይ ሻምፒዮን ለመሆን በቅታለች፡፡
እንዲሁም በፈረንጆቹ 1982 ለሦስተኛ ጊዜ ያሸነፈች ሲሆን÷ ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫውን ያሳካችው በፈረንጆቹ 2006 ነበር፡፡
የአራት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ሀገር ጣሊያን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨምሮ ለተከታታይ ሦስተኛ ጊዜ ከውድድሩ ውጪ የሆነች ሲሆን÷ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችው በፈረንጆቹ 2014 ነበር፡፡
ከዚያ በኋላ ማጣሪያውን ማለፍ ባለመቻሏ ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ ከመድረኩ ውጪ ሆናለች፡፡
ሌላኛዋ አራት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያሸነፈችው ሀገር ጀርመን ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን የሆነችው በ1954 ነበር፡፡
ከዚያ በኋላ በፈረንጆቹ 1974፣ 1990 እና 2014 ላይ በመድረኩ ሻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል፡፡
የደቡብ አሜሪካዋ ሀገር አርጀንቲና ደግሞ ሦስት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት ችላለች፡፡
አርጀንቲና ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻለችው በፈረንጆቹ 1978 እንደነበር ይታወሳል፡፡
በፈረንጆቹ 1986 ለሁለተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆነች በኋላ ከ36 ዓመታት ጥበቃ በኋላ በ2022 ለ3ኛ ጊዜ ማሸነፏ ይታወሳል፡፡
ፈረንሳይ እና ዩራጋይ ደግሞ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻሉ ብሔራዊ ቡድኖች ናቸው፡፡
ዩራጋይ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ውድድር ያሸነፈች ሲሆን÷ ወቅቱም በፈረንጆቹ 1930 ነበር፡፡
የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ውድድር ያሸነፈችው ዩራጋይ በወቅቱ ውድድሩን ያዘጋጀችው ራሷ እንደነበረች ይታወሳል፡፡
ዩራጋይ ከዚያ በኋላ በፈረንጆቹ 1950 በድጋሚ ዋንጫውን ማንሳቷ አይዘነጋም፡፡
ፈረንሳይ በፈረንጆቹ 1998 እና 2018 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ ሁለት ጊዜ ከዋንጫው ጋር ተገናኝታለች፡፡
እንግሊዝ እና ስፔን ደግሞ በተመሳሳይ አንድ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
እንግሊዝ በፈረንጆቹ 1966 ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን ያሳካች ሲሆን÷ በወቅቱም የውድድሩ አዘጋጅ ሀገር ራሷ ነበረች፡፡
ከዚያ በኋላ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በመድረኩ ሻምፒዮን መሆን አልቻለም፡፡
ስፔን በፈረንጆቹ 2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪኳ ሻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል፡፡
የፊታችን ሐሙስ በሚጀምረው የ2026 ዓለም ዋንጫ አዲስ ሀገር ሻምፒዮን ይሆናል ወይስ ከዚህ ቀደም ካነሱ ሀገራት መካከል አንዱ ሻምፒዮን ይሆናል የሚለው ይጠበቃል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
6 days ago