(ዘ-ሐበሻ ዜና) ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ የእስራኤል ባለስልጣን በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተደረገ ባለው ስምምነት ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ስጋት ገልጸዋል። ባለስልጣኑ ለቻናል 12 የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፣ አሁን እየተረቀቀ ያለው ስምምነት "መጥፎ" መሆኑን ተናግረዋል።
የስምምነቱ ማዕቀፍ ቴህራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ከኒውክሌር መሳሪያ ባልተናነሰ መልኩ እንደ ጦር መሳሪያ አድርጋ መጠቀም እንደምትችል የሚያሳይ እና የሚያስተምር መሆኑን ባለስልጣኑ አስረድተዋል።
እነዚህ ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን አክለውም፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በኢኮኖሚ ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን ያምናሉ ብለዋል።
ይህም ማለት በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ምንም አይነት የድርድር ለውጥ እና ማቋረጫ ላይ ሳይደረስ ይህን ወሳኝ የዓለም የውሃ ላይ መስመር (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን) ክፍት ለማድረግ እንደሚያስችል ፕሬዝዳንቱ ማሰባቸውን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ባለስልጣኑ ለዜና አውታሩ እንደገለጹት፣ ይህ የመጀመርያው የስምምነት ምዕራፍ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ደረጃ ምን ሊሆን እንደሚችል እስካሁን ምንም የታወቀና ግልጽ የሆነ ነገር የለም።
የስምምነቱ ማዕቀፍ ቴህራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ከኒውክሌር መሳሪያ ባልተናነሰ መልኩ እንደ ጦር መሳሪያ አድርጋ መጠቀም እንደምትችል የሚያሳይ እና የሚያስተምር መሆኑን ባለስልጣኑ አስረድተዋል።
እነዚህ ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን አክለውም፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በኢኮኖሚ ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን ያምናሉ ብለዋል።
ይህም ማለት በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ምንም አይነት የድርድር ለውጥ እና ማቋረጫ ላይ ሳይደረስ ይህን ወሳኝ የዓለም የውሃ ላይ መስመር (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን) ክፍት ለማድረግ እንደሚያስችል ፕሬዝዳንቱ ማሰባቸውን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ባለስልጣኑ ለዜና አውታሩ እንደገለጹት፣ ይህ የመጀመርያው የስምምነት ምዕራፍ ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጣዩ ደረጃ ምን ሊሆን እንደሚችል እስካሁን ምንም የታወቀና ግልጽ የሆነ ነገር የለም።
12 days ago