Logo
SeledaPost
በኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች በሕዝብ አውቶብስ ላይ ተኩስ በመክፈት ተሳፋሪዎችን አገቱ

በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ ወደ ፍቼ በሚወስደው መንገድ አሊደሮ በተባለ አካባቢ ታጣቂዎች ሕዝብ ጭኖ እየተጓዘ በነበረ ልዩ የሕዝብ አውቶብስ ላይ ተኩስ በመክፈትና ተሽከርካሪውን አስገድደው በማስቆም ከሦስት ሰዎች በቀር ሁሉንም ተሳፋሪዎች አፍነው መውሰዳቸውን የካቢኔ ሹፌሮች ገለጹ።

የአውቶብሱን መስታወትና ጎማዎች በመምታት የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት ተከትሎ፣ አካባቢው ለዓመታት የታጠቁ ወንበዴዎች እገታ፣ ዘረፋና ግድያ የሚፈጽሙበት ቢሆንም በጉዳቱ ግዝፈት ልክ ትኩረት እንዳልተሰጠው የተጠቆመ ሲሆን፤ የሕግ አስከባሪዎች ተሳፋሪዎችን ለማዳን ሕይወታቸውን ጭምር እየከፈሉ መሆኑ ቢመሰገንም፣ የአፈና ወንጀሉን ከስር መሰረት ለመንቀልና ሾፌሮችን፣ ረዳቶችንና ተሳፋሪዎችን ከአደጋ ለመጠበቅ የአሠራር ግምገማ በማድረግ አዳዲስ ስልቶችን መከተልና በቂ ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

seledadotio
seledadotio
17 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.