ምክር ቤቱ 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል
*****************
6ኛው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል።
ምክር ቤቱን 18ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ረፐብሊክ እንዲሁም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተደረገውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ለማጽደቅ የቀረቡ አራት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ የሚመራ ይሆናል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ይመራል።
በመጨረሻ ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ የሚመራ ሲሆን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት መርምሮ እንደሚያፀድቅም የሚጠበቅ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ebc #ethiopia #hopr
*****************
6ኛው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል።
ምክር ቤቱን 18ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ረፐብሊክ እንዲሁም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተደረገውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ለማጽደቅ የቀረቡ አራት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ የሚመራ ይሆናል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ይመራል።
በመጨረሻ ምክር ቤቱ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ የሚመራ ሲሆን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት መርምሮ እንደሚያፀድቅም የሚጠበቅ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ebc #ethiopia #hopr
1 month ago