Logo
SeledaPost
በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ሦስት ኢትዮጵያዊያን በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት እና የአገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ ትናንት የተገደሉት በጆሀንስበርግ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ማክዶናልድ በሚባለው የፈጣን ምግቦች መሸጫ ውስጥ በመመገብ ላይ እንዳሉ ነው ፡፡ ጥቃቱ የተፈፀመው መጤ ጠል አራማጅ ደቡብ አፍሪካዊያን በስደተኞች ላይ ተቃውሞ ለማሰማት የሠልፍ ጥሪ እያደረጉ ባሉበት ወቅት ነው ፡፡

አንድ የአገሪቱ ፖሊስ መኮንን ግን ግድያው ኢትዮጵያዊያኑ እርስ በእርስ ባለቸው መጠቃቃት የተፈጸመ ሳይሆን እንዳልቀረ ጥርጣሬውን ገልጿል፡፡በጥቃቱ ሁለት ናይጄሪያውያንም ተገድለዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተደረገበት ቀን መታሰቢያ በሆነው እና በየዓመቱ በጎርጎሪያኑ ሚያዚያ 27 ቀን በሚከበረው የነፃነት ቀን ነው።Via DW

seledadotio
seledadotio
2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.