Logo
Getu Temesgen
የኦሮሚያ ባንክ የፋሲካ በዓል ስጦታ፦ ለ7 ግብረሰናይ ድርጅቶች የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ! 🇪🇹✨

​ኦሮሚያ ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አሳይቷል። የዘንድሮውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ለሚረዱ 7 ሀገር በቀል ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

​የድጋፉ ዝርዝር፦

​የኢኦተቤ የልማትና ተራድኦ ኮሚሽን፦ 1,000,000 ብር

​አበበች ጎበና በጎ አድራጎት ድርጅት፦ 1,000,000 ብር

​የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት፦ 1,000,000 ብር

​የአዲስ አበባ ከተማ የምገባ ማዕከል፦ 500,000 ብር

​ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት፦ 500,000 ብር

​ተስፋ አዲስ (የህጻናት ካንሰር ህሙማን)፦ 500,000 ብር

​ሰበታ የአይነ ስዉራን ትምህርት ቤት፦ 500,000 ብር

​የባንኩ መልዕክት፦

የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኦቦ ተፈሪ መኰንን እንደገለጹት፣ ይህ ድጋፍ ለበዓል መዋያ ብቻ ሳይሆን ተረጂ ወገኖቻችን ቀጣይ ህይወታቸው የሚሻሻልበት እንዲሆን የታለመ ነው። ባንኩ ከዚህ ቀደም የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ መሰል ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል።

​በጎነት ለራስ ነው!
ለኦሮሚያ ባንክ ምስጋና ይገባዋል። 🙏

​#getu #oromiabank #csr #ethiopia #charity #easterdonation #socialresponsibility #abebechgobena #kidneydialysis #cancersupport #ኦሮሚያባንክ #በጎአድራጎት #ፋሲካ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.