Logo
Getu Temesgen
ጣሊያን የቤት እንስሳ ለሞተበት ሠራተኛ ሶስት ቀን የሐዘን ፈቃድ ልትሰጥ ነው
#ethiopia | ​በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።

ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።

ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።

ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።

56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ላ_ሪፐብሊካ #internationalbusiness #italy #fidelpost #economynews #internetsafety

2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.