Logo
Getu Temesgen
አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካንውያን ሆይ አትጨነቁ እያሉ ነው
#ethiopia | በአፍሪካዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ባለቤትነት የሚመራው ግዙፉ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለተለያዩ የአፍሪካ አገራት የነዳጅ ኤክስፖርት መጀመሩን አስታወቀ። ፋብሪካው 456 ቶን ነዳጅ ለሽያጭ ያቀረበ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ ገዢዎችም አይቮሪ ኮስት፣ ካሜሮን፣ ታንዛንያ እና ቶጎ መሆናቸው ተገልጿል።

በናይጄሪያ የሚገኘው ይህ ማጣሪያ በቀን 650 ሺህ በርሜል ነዳጅ የማጣራት አቅም ያለው ሲሆን፣ የናይጄሪያን ፍላጎት አሟልቶ ለውጭ ገበያ የሚተርፍ ምርት እያመረተ ይገኛል።

በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭት ምክንያት የተከሰተውን የኃይል አቅርቦት እጥረት እና የዋጋ ንረት ለመቋቋም ኤክስፖርቱ በአፋጣኝ እንዲጀመር ተደርጓል።

ይህ ጅምር ለምስራቅ፣ ምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ አገራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ ሆኗል።

ፋብሪካው በ2024 ሥራ ከመጀመሩ በፊት ናይጄሪያ የነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ በሙሉ ከውጭ በማስገባት ታሟላ ነበር፤ አሁን ግን ላኪ መሆን ችላለች።

የፋብሪካው ቃል አቀባይ እንደገለጹት ከአፍሪካ አገራት በተጨማሪ ከሌሎች አህጉራትም ከፍተኛ የነዳጅ ፍላጎት እየቀረበላቸው ይገኛል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #dangoterefinery #alikodangote #nigeriaeconomy #africaenergy #fuelexport #oilandgas #economicintegration #africanewsupdate

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.