የኢትዮ- ጣሊያን የኮንስትራክሽንና የመሰረተ ልማት ፎረም ተጀመረ
#ethiopia | ዛሬ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ መልሶ ማልማት ፎረም ተጀመረ።
ፎረሙ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ ሚኒስትሮች እና የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርና የዓለምቀፍ ትብብር ሀላፊ ማሪያ ትሪፖዲ በተገኙበት ተጀምሯል።
አሁን ላይ በመዲናችን የንግድ እንቅስቃሴ እያደገ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰቱም በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ እንደተናገሩት አዲስ አበባ በፍጥነት እየተለወጠች በመሆኗ፣ ይህ የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ መልሶ ማልማት ፎረም መካሄዱ ወቅታዊ፣ ትክክለኛና እጅግ አስፈላጊ ነው።
የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያጠናክሩበት ፎረም ተካሄደ።
መጋቢት 16 ቀን 2018 አ.ም የኢትዮጵያን የመሠረተ ልማት አድማስ የሚያሰፋና የከተማ ውበት ሽግግርን ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ የታመነበት የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሠረተ ልማት እና የከተማ ተሃድሶ ፎረም ተከፍቷል።
ይህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው መድረክ፥በጣሊያን የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር (MAECI) አዘጋጅነት የተሰናዳ ሲሆን፥ በጣሊያን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በመድረኩ ላይ ተገኝቷል።
ፎረሙ የጣሊያንን ዘመናዊ የምህንድስና ጥበብ እና የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ልምድ ከኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት ጋር ለማስተሳሰር ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ ከ25 በላይ ግዙፍ የጣሊያን ኩባንያዎች እና የኢንዱስትሪ ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል::
ቀልጣፋ የትራንስፖርት ትስስር መፍጠር ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ መስራት እንዲሁም ዘላቂ የኃይልና የውሃ አቅርቦት ግንባታን ማፋጠን የግንኙነቱ ዋና አላማ ነው።
ይህ መድረክ የሁለቱን አገራት የቆየ ግንኙነት ወደ ላቀ የንግድና የኢንቨስትመንት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ጠንካራ ድልድይ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ እና የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#getutemesgen #ehpea #horticultureethiopia #economynews #ethiopianexports #hortiflora2026 #flowerindustry
#ethiopia | ዛሬ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ መልሶ ማልማት ፎረም ተጀመረ።
ፎረሙ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ ሚኒስትሮች እና የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርና የዓለምቀፍ ትብብር ሀላፊ ማሪያ ትሪፖዲ በተገኙበት ተጀምሯል።
አሁን ላይ በመዲናችን የንግድ እንቅስቃሴ እያደገ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰቱም በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ እንደተናገሩት አዲስ አበባ በፍጥነት እየተለወጠች በመሆኗ፣ ይህ የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ መልሶ ማልማት ፎረም መካሄዱ ወቅታዊ፣ ትክክለኛና እጅግ አስፈላጊ ነው።
የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያጠናክሩበት ፎረም ተካሄደ።
መጋቢት 16 ቀን 2018 አ.ም የኢትዮጵያን የመሠረተ ልማት አድማስ የሚያሰፋና የከተማ ውበት ሽግግርን ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ የታመነበት የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሠረተ ልማት እና የከተማ ተሃድሶ ፎረም ተከፍቷል።
ይህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው መድረክ፥በጣሊያን የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር (MAECI) አዘጋጅነት የተሰናዳ ሲሆን፥ በጣሊያን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በመድረኩ ላይ ተገኝቷል።
ፎረሙ የጣሊያንን ዘመናዊ የምህንድስና ጥበብ እና የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ልምድ ከኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት ጋር ለማስተሳሰር ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ ከ25 በላይ ግዙፍ የጣሊያን ኩባንያዎች እና የኢንዱስትሪ ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል::
ቀልጣፋ የትራንስፖርት ትስስር መፍጠር ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ መስራት እንዲሁም ዘላቂ የኃይልና የውሃ አቅርቦት ግንባታን ማፋጠን የግንኙነቱ ዋና አላማ ነው።
ይህ መድረክ የሁለቱን አገራት የቆየ ግንኙነት ወደ ላቀ የንግድና የኢንቨስትመንት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ጠንካራ ድልድይ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ እና የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#getutemesgen #ehpea #horticultureethiopia #economynews #ethiopianexports #hortiflora2026 #flowerindustry
2 months ago