Logo
FIDEL POST NEWS
የሴት አናኮንዳ እባቦች ከወንዱ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ካደረጉ በኋላ ወንዱን አንቀው በመግደል ይበሉታል

ተመራማሪዎች ይህን አስደንጋጭ የሚመስል ድርጊት ከህልውና ጋር የተያያዘ መሆኑ ይጠቁማሉ።

​ሴት አናኮንዳዎች በርግዝና ወቅት ለሰባት ወራት ያህል ያለምንም ምግብ ይጾማሉ።

በዚህ ረጅም የጾም ጊዜ ውስጥ ራሳቸውንና በሆዳቸው ውስጥ ያሉትን ፅንሶች ለማቆየት የሚያስፈልጋቸውን ከፍተኛ ኃይል ለማግኘት ወንዱን አድነው ይበሉታል።

ወንዱ አናኮንዳ ከሴቷ ጋር ሲነጻጸር መጠኑ አነስተኛ በመሆኑ ለሴቷ ጠቃሚ የፕሮቲን ምንጭ ሆኖ ያገለግላል።

ይህ ተፈጥሯዊ ሂደት ዝርያቸው እንዲቀጥል የሚረዳ የህልውና ዘዴ እንደሆነ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ።

​ምንጭ፦ National Geographic, Science Focus, Live Science
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.