ጣሊያንን ጨምሮ አዳዲስ ሀገራት የኢትዮጵያውያን የሥራ መዳረሻ ሆኑ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባወጣው የሰባት ወራት የሥራ ክንውን ሪፖርት መሠረት፣ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ዘርፍ አዳዲስና ተስፋ ሰጪ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል።
ዕቅድን ያለፈ አፈጻጸም፦ ባለፉት ሰባት ወራት 435 ሺህ ዜጎችን ለማሰማራት ታቅዶ፣ ዕቅዱን በማለፍ ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች በውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል።
አዳዲስ መዳረሻ ሀገራት፦ መንግሥት ከነባር አምስት ሀገራት በተጨማሪ ጣሊያንን ጨምሮ አራት አዳዲስ ሀገራትን የሥራ መዳረሻ በማድረግ የስምሪት አማራጮችን አስፍቷል።
የባለሙያዎች ስምሪት፦ ስምሪቱ ከቤት ውስጥ ሥራ ባለፈ፣ የሰለጠኑ እና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ያካተተ ነው። ይህም በሁለትዮሽ ድርድር የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑ ተገልጿል።
ቀጣይ ድርድሮች፦ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK)፣ ከኢራቅ እና ከኦማን ጋር የሚደረጉ የሥራ ስምሪት ድርድሮች ከጫፍ መድረሳቸው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ባለፉት ሰባት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባወጣው የሰባት ወራት የሥራ ክንውን ሪፖርት መሠረት፣ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ዘርፍ አዳዲስና ተስፋ ሰጪ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል።
ዕቅድን ያለፈ አፈጻጸም፦ ባለፉት ሰባት ወራት 435 ሺህ ዜጎችን ለማሰማራት ታቅዶ፣ ዕቅዱን በማለፍ ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች በውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል።
አዳዲስ መዳረሻ ሀገራት፦ መንግሥት ከነባር አምስት ሀገራት በተጨማሪ ጣሊያንን ጨምሮ አራት አዳዲስ ሀገራትን የሥራ መዳረሻ በማድረግ የስምሪት አማራጮችን አስፍቷል።
የባለሙያዎች ስምሪት፦ ስምሪቱ ከቤት ውስጥ ሥራ ባለፈ፣ የሰለጠኑ እና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ያካተተ ነው። ይህም በሁለትዮሽ ድርድር የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑ ተገልጿል።
ቀጣይ ድርድሮች፦ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK)፣ ከኢራቅ እና ከኦማን ጋር የሚደረጉ የሥራ ስምሪት ድርድሮች ከጫፍ መድረሳቸው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ባለፉት ሰባት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
3 months ago