Logo
FIDEL POST NEWS
ጣሊያንን ጨምሮ አዳዲስ ሀገራት የኢትዮጵያውያን የሥራ መዳረሻ ሆኑ

​የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባወጣው የሰባት ወራት የሥራ ክንውን ሪፖርት መሠረት፣ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ዘርፍ አዳዲስና ተስፋ ሰጪ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል።

​ዕቅድን ያለፈ አፈጻጸም፦ ባለፉት ሰባት ወራት 435 ሺህ ዜጎችን ለማሰማራት ታቅዶ፣ ዕቅዱን በማለፍ ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች በውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል።

​አዳዲስ መዳረሻ ሀገራት፦ መንግሥት ከነባር አምስት ሀገራት በተጨማሪ ጣሊያንን ጨምሮ አራት አዳዲስ ሀገራትን የሥራ መዳረሻ በማድረግ የስምሪት አማራጮችን አስፍቷል።

​የባለሙያዎች ስምሪት፦ ስምሪቱ ከቤት ውስጥ ሥራ ባለፈ፣ የሰለጠኑ እና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ያካተተ ነው። ይህም በሁለትዮሽ ድርድር የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑ ተገልጿል።

​ቀጣይ ድርድሮች፦ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK)፣ ከኢራቅ እና ከኦማን ጋር የሚደረጉ የሥራ ስምሪት ድርድሮች ከጫፍ መድረሳቸው ተጠቁሟል።

​በአጠቃላይ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ባለፉት ሰባት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል።

​ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.