የዓለም የቡና ገበያ መናወጥ፦ የኢትዮጵያ ላኪዎች 'ምርታችሁን ቶሎ ሽጡ' ተባሉ
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን ተከትሎ፣ አቅራቢዎችና ላኪዎች ምርታቸውን በፍጥነት ለገበያ እንዲያቀርቡ አሳሰበ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ እንደገለጹት፣ ባለፉት ሁለት ወራት የቡና ዋጋ ከ4 ዶላር ወደ 2.8 ዶላር ዝቅ ብሏል።
ዋጋው በቀጣይም እስከ 2.5 ዶላር ሊወርድ ስለሚችል፣ ባለድርሻ አካላት ምርቱን አከማችተው ለከፍተኛ ኪሳራ እንዳይዳረጉ ጥሪ ቀርቧል።
በበጀት ዓመቱ 600 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ ውጤታማ ለመሆንም ላኪዎች በስፔሻሊቲ ቡና ጥራት ላይ እንዲያተኩሩ ተጠይቋል።
በተጨማሪም ቡናን ከአንድ ዓመት በላይ ማከማቸት ወይም በኮንትሮባንድ መሸጥ በሕግ እንደሚያስቀጣ ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
ዘገባው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን ተከትሎ፣ አቅራቢዎችና ላኪዎች ምርታቸውን በፍጥነት ለገበያ እንዲያቀርቡ አሳሰበ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ እንደገለጹት፣ ባለፉት ሁለት ወራት የቡና ዋጋ ከ4 ዶላር ወደ 2.8 ዶላር ዝቅ ብሏል።
ዋጋው በቀጣይም እስከ 2.5 ዶላር ሊወርድ ስለሚችል፣ ባለድርሻ አካላት ምርቱን አከማችተው ለከፍተኛ ኪሳራ እንዳይዳረጉ ጥሪ ቀርቧል።
በበጀት ዓመቱ 600 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ ውጤታማ ለመሆንም ላኪዎች በስፔሻሊቲ ቡና ጥራት ላይ እንዲያተኩሩ ተጠይቋል።
በተጨማሪም ቡናን ከአንድ ዓመት በላይ ማከማቸት ወይም በኮንትሮባንድ መሸጥ በሕግ እንደሚያስቀጣ ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
ዘገባው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው
3 months ago