Logo
SeledaPost
BRAKiNG ኢራን በዱባይ የሚገኘው የአሜሪካ ቆንስላ በሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ተመታ

​ዛሬ ምሽት ላይ በዱባይ የሚገኘው የአሜሪካ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት እንደደረሰበት ተዘገበ።

ጥቃቱን ተከትሎ በቆንስላው ህንጻ ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ የተነሳ ሲሆን፣ ጥቁር ጭስ ከሩቅ ቦታዎች እንደሚታይ ሲኤንኤን ያረጋገጣቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎች ያሳያሉ።

​ጥቃቱ የተሰነዘረው በኢራን ድሮን እንደሆነ በስፋት እየተጠረጠረ ይገኛል። ይህ ክስተት በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ቀውስ አካል ተደርጎ ተወስዷል።

በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም በተመሳሳይ የድሮን ጥቃት መመታቱ የተገለጸ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለድርጊቱ አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጡ ዝተዋል።

እስካሁን ስለደረሰው የሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃ አልወጣም።

seledadotio
seledadotio
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.