Logo
FIDEL POST NEWS
ኢራን በሳውዲ አረቢያ ላይ ጥቃት ሰነዘረች

ኢራን በሳውዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ እና በምስራቃዊ ግዛት ላይ ጥቃት መሰንዘሯን የሳውዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሪያድ ጥቃቱ መክሸፉን የገለጸች ሲሆን፥ ድርጊቱን ኮንነዋለች።

​ሳውዲ አረቢያ የአየር ክልሏን ለማንኛውም ወታደራዊ ኦፕሬሽን እንደማትፈቅድ ቀደም ብላ ብታሳውቅም ጥቃቱ መፈጸሙ ተገልጿል።

አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሳልማን ከጎረቤት አረብ አገራት መሪዎች ጋር በመወያየት ቀጣናዊ አንድነትን ጠይቀዋል።

ሳውዲ ራሷን የመከላከል እና የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብቷ የተጠበቀ መሆኑን አስጠንቅቃለች።

ይህ ጥቃት በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.