Logo
FIDEL POST NEWS
በጣሊያን አነጋጋሪ የሆነው "የሜሎኒ መልክ ያለው መልአክ" ተፋቀ!

​በጣሊያን ሮም በሚገኝ አንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኝ የመልአክ ስዕል (Fresco) የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒን እንዲመስል ተደርጎ መሳሉ ታላቅ ውዝግብ አስነሳ።

​የታሪኩ ዝርዝር፦
​ክስተቱ፦ በቅዱስ ላውረንስ ባሲሊካ ውስጥ የሚገኝ የመልአክ ስዕል እድሳት ሲደረግለት፣ መልኩ የ49 ዓመቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒን ፍጹም በሚመስል መልኩ ተቀይሮ ተገኝቷል።

​ተቃውሞው፦ ይህ ድርጊት በፖለቲከኞች እና በሀይማኖት መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። የሮም ሀገረ ስብከት የሆኑት ካርዲናል ባልዶ ሬይና "የክርስትና ጥበብ ለፖለቲካ መጠቀሚያ መሆን የለበትም" ሲሉ አውግዘዋል።

​የተወሰደ እርምጃ፦ በካህናቱ ትዕዛዝ መሰረት የስዕሉ ፊት ዛሬ እንዲፋቅ ተደርጓል። ሰዓሊው ብሩኖ ቫለንቲኔቲ በቫቲካን ትዕዛዝ መሰረት ፊቱን ማጥፋቱን ገልጿል።

​ምክንያቱ፦ የቤተክርስቲያኑ ፓስተር ዳኒኤል ሚኬሌቲ ሲናገሩ "ሰዎች ጸሎት ከማድረስ ይልቅ ስዕሉን ለማየት መሰለፋቸው ተቀባይነት የለውም" ብለዋል።

​ሜሎኒ ምን አለች? 🤷‍♀️
ጠቅላይ ሚኒስትሯ በኢንስታግራም ገጿ ላይ የስዕሉን ፎቶ በመለጠፍ "አይ፣ እኔ በእርግጠኝነት መልአክ አልመስልም" በማለት ነገሩን በፈገግታ አልፋዋለች።
​የጣሊያን የባህል ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.