Logo
FIDEL POST NEWS
የ"ደም እንባ" ሴራ ተጋለጠ፦ በድንግል ማርያም ስም ያታለለችው ግለሰብ ፍርድ ቤት ቀረበች

​በጣሊያን ትሬቪኛኖ ከተማ ለዓመታት "ድንግል ማርያም ተገለጥልኛለች" በማለት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ስታታልል የቆየችው ጂሴላ ካርዲያ በመጪው ሚያዝያ ወር የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቃት ተረጋገጠ።

​የማንነት ስውር ሴራ፦ የካርዲያ ትክክለኛ ስም ማሪያ ጁሴፔ ስካርፑላ ሲሆን፣ ወደ ትሬቪኛኖ ከመምጣቷ በፊት በሲሲሊ በንግድ ማጭበርበር ወንጀል የሁለት ዓመት የገደብ እስራት ተፈርዶባት የነበረች መሆኑ ተጋልጧል።
​የ"ደም እንባ" ምስጢር፦ ካርዲያ ከቦስኒያ (ሜዲጎርዬ) የገዛችው ሃውልት "የደም እንባ ያፈሳል" ብላ ብታስተዋውቅም፣ የፖሊስ ምርመራ ግን በሃውልቱ ላይ የታየው ደም የሰው (ምናልባትም የራሷ) ደም ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬዎችን አስነስቷል።

​የፍርሃት ስብከት፦ ተከሳሿ ሰዎችን ለማስፈራራትና ገንዘብ ለማሰባሰብ ስትል "ታላላቅ የመሬት መንቀጥቀጦች ይከሰታሉ"፣ "ሰይጣን ቤተክርስቲያንን ሊቆጣጠር ነው" እና "ኮሙኒዝም ካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ይወርራል" የሚሉ የሀሰት ትንቢቶችን ትነዛ ነበር።

​የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘዴው፦ በየወሩ መጀመሪያ በብራቺያኖ ሀይቅ አጠገብ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በመሰብሰብ ድራማዊ ትዕይንቶችን ታሳያለች። በተጨማሪም ድህረ-ገጽ በመክፈት በአለም ዙሪያ ካሉ ምዕመናን 365,000 ዩሮ (ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ) በልገሳ ስም ሰብስባለች።

​የቤተክርስቲያን የመጨረሻ ውሳኔ፦ ቫቲካን ባደረገችው ጥናት "ምንም አይነት ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ተአምር የለም" በማለት ድርጊቱን በይፋ አውግዛለች።

ካርዲያ እና ባለቤቷ "በከባድ ማጭበርበር" ወንጀል ተከሰው ሚያዝያ 7 ቀን በሲቪታቬቺያ ፍርድ ቤት ለፍርድ ይቀርባሉ። ሃውልቱም በፖሊስ እና በቤተክርስቲያን ትዕዛዝ ከቦታው ተነስቷል።
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.