ፈረንሳይ ከ15 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የማኅበራዊ ሚዲያ እገዳን አጸደቀች
የፈረንሳይ ብሔራዊ ምክር ቤት ከ15 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን የሚከለክል ረቂቅ ሕግ በድምፅ ብልጫ ማጽደቁን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አስታወቁ።
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እንደገለጹት፤ ይህ ርምጃ በሳይንሳዊ ጥናትና በሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፤ እንደ ስናፕቻት፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ያሉ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን መጠቀምን ይከለክላል።
ውሳኔው የተላለፈው ማኅበራዊ ሚዲያ በሕፃናት አእምሮ ጤና ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል።
ፈረንሳይ ከዚህ ቀደም መሰል የዕድሜ ገደብ ለመጣል ሞክራ በአውሮፓ ሕብረት ደንቦች ምክንያት ሳይሳካላት መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፤ አሁን የጸደቀው ሕግ ከአውስትራሊያ ሕግ ጋር ይመሳሰላል።
ይህ አዲስ ሕግ የሕፃናትን ደኅንነት ለመጠበቅና በማኅበራዊ ሚዲያ ሱሰኝነት የሚመጡ የጤና ችግሮችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ኢማኑኤል ማክሮን አመልክተዋል።
Gazette Plus
የፈረንሳይ ብሔራዊ ምክር ቤት ከ15 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን የሚከለክል ረቂቅ ሕግ በድምፅ ብልጫ ማጽደቁን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አስታወቁ።
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እንደገለጹት፤ ይህ ርምጃ በሳይንሳዊ ጥናትና በሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፤ እንደ ስናፕቻት፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ያሉ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን መጠቀምን ይከለክላል።
ውሳኔው የተላለፈው ማኅበራዊ ሚዲያ በሕፃናት አእምሮ ጤና ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል።
ፈረንሳይ ከዚህ ቀደም መሰል የዕድሜ ገደብ ለመጣል ሞክራ በአውሮፓ ሕብረት ደንቦች ምክንያት ሳይሳካላት መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፤ አሁን የጸደቀው ሕግ ከአውስትራሊያ ሕግ ጋር ይመሳሰላል።
ይህ አዲስ ሕግ የሕፃናትን ደኅንነት ለመጠበቅና በማኅበራዊ ሚዲያ ሱሰኝነት የሚመጡ የጤና ችግሮችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ኢማኑኤል ማክሮን አመልክተዋል።
Gazette Plus
5 months ago