Logo
FIDEL POST NEWS
"ጦርነት እንደ ፋሽን ተመልሷል" — ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ

​የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በዓለም ላይ እየታየ ባለው የግጭትና የጥቃት ዝንባሌ ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ስጋት ገለጹ።

​ጳጳሱ በቫቲካን ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ባደረጉት ንግግር የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል፡-

​ስለ ጦርነት መስፋፋት፦ "ጦርነት እንደ ፋሽን ተመልሷል፤ የጦርነት ስሜትም በዓለም ላይ እየተስፋፋ ነው" ብለዋል።

​የዲፕሎማሲ መዳከም፦ በሀገራት መካከል የሚደረግ የጋራ ውይይት (Multilateralism) እየተዳከመ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

​የጉልበት ዲፕሎማሲ፦ በውይይትና በስምምነት ላይ የተመሰረተ ዲፕሎማሲ እየቀረ፣ በግለሰብ ሀገራት ወይም በሀይለኛ ጥመኞች የሚመራ "የጉልበት ዲፕሎማሲ" እየተተካ መሆኑን አስረድተዋል።

​የድንበር መጣስ፦ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የጸደቀውና "የሌላን ሀገር ድንበር በኃይል መጣስን የሚከለክለው" መርህ መጣሱንም ወቅሰዋል።

​ልዩ ሁኔታ፦
ለመጀመሪያ ጊዜ ከአሜሪካ የተመረጡት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ፣ በተለመደው የጣሊያንኛ ወይም የፈረንሳይኛ ቋንቋ ፈንታ ንግግራቸውን በእንግሊዝኛ ማድረጋቸው ልዩ አድርጎታል።

​ጳጳሱ በንግግራቸው ወቅት ሰላም እንደ ተፈላጊ ስጦታ መታየቱ ቀርቷል ሲሉ በሀዘን ገልጸዋል።
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.