ኢትዮጵያ በሸፍጥ ያጣችውን የባህር በር ለመመለስ እየተሰራ ነው
ኢትዮጵያ በሸፍጥ ያጣችውን የባህር በር ለመመለስ እየተሰራ ነው ሲሉ የጨፌ ኦሮሚያ አፈጉባዔ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለጹ።
47ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድረክ ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው።
የጨፌ ኦሮሚያ አፈጉባዔ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን እንደገለጹት፤ በፌዴራሊዝም ሥርዓት ጥላ ሥር ለሁሉም የምትሆን እና ሁሉም የሚኖርባት አገር ለመገንባት እየተሰራ ነው።
ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አገር ናትም ነው ያሉት አፈ-ጉባኤዋ።
የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በህብረት ለመኖር የተወሰነበት ቀን መሆኑን ተናግረዋል።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አሻራ የተሳካ መሆኑን የገለጹት አፈጉባኤዋ፤ መንግሥት ኢትዮጵያ በሸፍጥ ያጣችውን የባህር በር ለመመለስ እየሰራ ነው ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ በበኩላቸው፤ የውይይት መድረኩ ዓላማ ምሁራን በአገረ መንግሥት ግንባታ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ የሚያስችል ነው።
ኢትዮጵያ ፈተናዎችን በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እያሸነፈች መሆኑን ጠቅሰው፤ ያደሩ ፈተናዎችን በምክክር ለመቅረፍም እየሰራች እንደሚገኝ ገልጸዋል።
Gazette Plus
ኢትዮጵያ በሸፍጥ ያጣችውን የባህር በር ለመመለስ እየተሰራ ነው ሲሉ የጨፌ ኦሮሚያ አፈጉባዔ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለጹ።
47ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድረክ ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው።
የጨፌ ኦሮሚያ አፈጉባዔ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን እንደገለጹት፤ በፌዴራሊዝም ሥርዓት ጥላ ሥር ለሁሉም የምትሆን እና ሁሉም የሚኖርባት አገር ለመገንባት እየተሰራ ነው።
ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አገር ናትም ነው ያሉት አፈ-ጉባኤዋ።
የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በህብረት ለመኖር የተወሰነበት ቀን መሆኑን ተናግረዋል።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አሻራ የተሳካ መሆኑን የገለጹት አፈጉባኤዋ፤ መንግሥት ኢትዮጵያ በሸፍጥ ያጣችውን የባህር በር ለመመለስ እየሰራ ነው ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ በበኩላቸው፤ የውይይት መድረኩ ዓላማ ምሁራን በአገረ መንግሥት ግንባታ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ የሚያስችል ነው።
ኢትዮጵያ ፈተናዎችን በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እያሸነፈች መሆኑን ጠቅሰው፤ ያደሩ ፈተናዎችን በምክክር ለመቅረፍም እየሰራች እንደሚገኝ ገልጸዋል።
Gazette Plus
7 months ago