Logo
SeledaPost
በካናዳ የመጀመሪያው ሙሉ አገልግሎት የሚሰጥ ነጻ የሸቀጣሸቀጥ መደብር ተከፈተ

ካናዳ ውስጥ የመጀመሪያው ሙሉ መጠን ያለው ነጻ የሸቀጣሸቀጥ መደብር በሬጂና፣ ሳስካችዋን፣ የሬጂና የምግብ ባንክ የማህበረሰብ የምግብ ማዕከል (Regina Food Bank’s Community Food Hub) አካል ሆኖ በሩን ከፈተ።

ይህ መደብር በሳምንት አምስት ቀናት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ እንደማንኛውም መደበኛ ሱፐርማርኬት፣ በመደርደሪያዎቹ ላይ ትኩስ ምርቶች፣ አስፈላጊ የምግብ ዓይነቶች እና የቤት ውስጥ እቃዎች ተደርድረው ይገኛሉ። ያለው ብቸኛው ልዩነት ሁሉም ነገር ነጻ መሆኑ ነው ተብሏል።

ገበያተኞች ቀድሞ ቀጠሮ ያስይዛሉ እና አስቀድሞ የታሸጉ ሳጥኖችን ከመቀበል ይልቅ የሚያስፈልጋቸውን ነገር ራሳቸው በመምረጥ ይወስዳሉ። የመደብሩ ዓላማ ክብርን፣ ምርጫንና ጤናማ የምግብ አማራጮችን ለቤተሰቦች መስጠት ሲሆን፣ የምግብ እርዳታን በተመለከተ ያለውን መገለል መቀነስ ነው ተብሏል።

የቀጠሮ ሥርዓቱ ፍትሐዊ ተደራሽነትን ከማረጋገጡም በላይ ቤተሰቦች በምቾትና በአክብሮት ግዢ እንዲፈጽሙ ያስችላቸዋል።

seledadotio
seledadotio
8 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.