Logo
SeledaPost
በደመወዝ ጭማሪ ሰበብ ዋጋ ያናሩ ከ57 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ተጨምሯል በሚል ሰበብ ዋጋ ያናሩ 57 ሺህ 212 ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግመዋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የንግድ ስርዓትና ላይሰንሲንግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤት አብዱል ሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ባቀረቡት ሪፖርት በሩብ ዓመቱ ንግድን ሥርዓት ለማስያዝ የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አብራርተዋል።

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ተጨምሯል በሚል ሰበብ ዋጋ ያናሩ 57 ሺህ ሺህ 212 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

seledadotio
seledadotio
10 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.