Logo
YenetaTube
በተራዘመዉ ጦርነት የፍልስጤም ክርስትያኖች 800 ብቻ ቀርተዋል !

ግብፅ በፍልስጤም የወደሙ መሳጂዶችን ዳግም ለመገንባት አዲስ አረብ ሀገራት የሚሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብያ ለማዘጋጀት ቃል መግባቷ ተሰምቷል አብያተክርስቲያናቱን ግን እስካሁን ዳግም ለመስራት አልተገኘም ።

በአንድ ወቅት አለምአቀፋዊው ጳጳሳዊ ፋውንዴሽን በዓለማች 38 አገሮች ውስጥ ክርስቲያኖች ስቃይና በደል እንዲሁም መገለል እንደሚደርስባቸው ከሰባቱ መካከል አንዱ ስቃይ መከራና ስደት እንደሚዳረግ
በጥናት አረጋግጧል ። ጥናቱ እንደገለፀው ከሆነ ደግሞ ክርስቲያኖች የሚገፉት የእምነቱ መፍለቂያ ከተባለው መካከለኛው ምስራቅ ነዉ ከቀዳሚዎቹ ደግሞ ፍልስጤም ትጠቀሳለች ።

እስኪ ለዛሬው እንደሌሉ ተቆጥረው ልሳን ቸግሯቸዉ በሁለት ጉልበተኞች መሃል ተገኝተው ህልዉናቸዉ አደጋ ላይ ስለሚገኘው የፍልስጤም ክርስትያኖችና አብያተክርስቲያናት ጥቂት ልበል ።

ፍልስጤም በጥንታዊ እና በዘመናዊው የመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ሚና ያለው አንድ አነስተኛ ክልል ነው። ለበርካታ የዓለማችን ዋና ዋና እምነቶች ካለው ጠቀሜታ እና በአፍሪካ እና እስያ መካከል ጠቃሚ የሆነ አገናኝ ድልድይ የሆነ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያለው በመሆኑ የፍልስጤም ታሪክ ተደጋጋሚ በሆነ ፖለቲካዊ ግጭት እና በአደገኛ የመሬት ወረራ የተሞላ ነው።

ይህ ሰርጥ ከግጭቱ በፊት በነበረ ቁጥራዊ መረጃ ከሆነ ሰፊውን ቁጥር የሚይዙት አረቦች ከዚህም ውስጥ በአብዛኛው የሱኒ ሙስሊም ሀይማኖት ተከታይ ቢሆንም ቅሉ ቀላል የማይባል አናሳ ክርስቲያኖች ይገኙበት ነበር።

የጋዛ ክርስቲያኖች ቁጥራቸው እምብዛም ባይሆንም እኒህ የጋዛ ክርስቲያኖች በቤተ-ክርስቲያኑ ዙሪያ ካለው መሬት ጋር ትልቅ ቁርኝት ስላላቸው ከጥንት እስከዛሬ እምነታቸው አስጠብቀው መዝለቅ ችለዉ ነበር ። ነገር ግን ከሁለት አመት በፊት አይ.ሁ..ዳዊ መሰረት ባላት እስራኤልና ከስሙ መነሻ ጀምሮ ለእስልምና እንደሚታገል የሚገልጸው ሃማስ ጦርነቱ ተቀሰቀሰ ።

በሀማስና እስራኤል በተራዘመ ጦርነት ምክንያት በ365 ስኩዌር ኪሎሜትር በ40 ኪሎሜትር የባህር እርዝማኔ ክልል ዉስጥ የምትገኘውን 2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ይኖሩባታል የተባለችዉን ጋዛ ሰርጥ የምድር ገሀነም ሆነች ሁለቱም ፅንፍ በመያዝ አፀፋ በሚመላለሱበት ወቅት በሁለቱም ዘንድ በሰላይነት የተፈረጁ እነዚህን ክርስትያኖች እና የእምነት ተቋማት ከቁብ የሚቆጥር ጠፋ ።

እስራኤል " የሐማስን መሪዎች ላይ ያነጣጠረ " እያለች በምትፈፅማቸዉ ንፁሃንን ከታጣቂዎች ያለየ ጥቃትና በሰማይ የቦንብ ዶፍም ሆነ ሃማስ ሰላይ ናችሁ በማለት በሚያደርስባቸዉ ማህበራዊ መገለል መፈጠራቸውን እስኪጠሉ መከራ ገጠማቸው ።
በዓለም ላይ ካሉት ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ በዓለም ላይ ካሉት ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ እንደሆነ የሚታመነዉ በ400 ዓ.ም አካባቢ በቅዱስ ፖርፊየስ እራሱ ባሰራው ቤተክርስትያን መሰረት ላይ እንደታነፀ የሚነገርለት በአለም ላይ ካሉ ጥንታዊ አብያተ ክርስትያናት አንዱ የሆነዉ በአለም ሶስተኛው ጥንታዊ ቤተክርስትያን ወደመ ።
የክርስቶስ የልደት ስፍራ በሆነችው የፍልስጥኤም ግዛት የዌስት ባንክ ከተማ ቤቴልሄም እና በጋዛ ሰርጥ የሚገኙ ክርስቲያኖች የልደቱን በዓል እንዲያከብሩ ተከለከሉ ሌሎችም አብያተክርስቲያናት እንዳልነበሩ ሆኑ ።

ምንድነው ማስረጃዎችህ ከተባልኩ አለምአቀፋዊ ሚዲያዎችን መጥቀስና ዘገባዎችን ማስታወስ ይቻላል ።

ለአለም አቀፍ የወንጀል ችሎት (ICC) የወንጀል ምርመራ ሪፖርት እንደገለፁት ከአምስት በላይ አብያተ ክርስቲያናት የ150 ዓመታት ታሪክን መዛግብትን ጨምሮ ተጎድተዋል ወይም ወድመዋል። ሲል ገልፆታል ።

በጋዛ የባህል ዘርፍ መጥፋት፣ ቤተመጻሕፍት እና የባህል ቅርሶች በመውደማቸው እንዳስደነገጣቸው ባለሙያዎቹ ተናግረዋል። "የፍልስጤም ማህበረሰብ መሰረቱ ወደ ፍርስራሽነት እየተቀየረ ነው፣ እናም ታሪካቸው እየጠፋ ነው።" ብለዉታል ።

በአለፉት ሁለት ዓመታት የጋዛ አነስተኛ ክርስቲያኖች መካከል 550 የሚጠጉ ሰዎች ከቤታቸዉ ከቤተክርስቲያን ተፈናቅለው
የመቃብር ሥፍራዎች ለመኖር ተገደዋል. ሲል ፎክስ ኒዉስ ዘግቧል ።

በጋዛ የሚኖሩ ክርስቲያኖች እስራኤል የምትፈፅመው ሞትና ውድመት እንዲያበቃ በመጸለይ የገናን በዓል አክብረዋል። በዌስት ባንክ ከተማ ቤተልሔም የኢየሱስ የትውልድ ቦታ በርካቶች ጸሎታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በእስራኤል “የዘር ማጥፋት” ሰለባዎችን በማስታወስ ፀሎት አድርገዋል። የሚለው ዘገባ የ ዋሽንግተን ፖስት ነዉ ።

በ2024 እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ከሚገኙት ሶስት አብያተ ክርስቲያናትን ሙሉ በሙሉ አፍርሳለች ሲል የግዛቱ ኢንዶውመንት ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ለአናዶሉ ተናግሯል።

ኢክራሚ አል ሙዳላል እንዳሉት የእስራኤል ጦር ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ግንኙነት ያላቸውን 255 የሀይማኖት አባቶች እና መግደሉን እና ሌሎች 26 ሰዎችን ማሰሩን ተናግረዋል። ብሏል የአናዶሉ ዘገባ

" የአምልኮ ቦታዎች ላይ በፀጥታ ሃይሎች ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ሁሉንም ቅድስናዎች፣አለም አቀፍ ህጎች እና የሰብአዊ መብት ህጎችን መጣስ ነው"ብለዋል።

በአውሮፓውያኑ 2024 ጥቅምት 19 አመሻሽ ገደማ ከእስራኤል የተወነጨፈ ሚሳዔል አንዱን የቤተ-ክርስቲያኑን ሕንፃ መታው። በጥቃቱ 18 ሰዎች ተገደሉ፤ በርካቶች ቆሰሉ።

ማሪያን እንደምትለው የ34 ዓመቱ የባሏ ወንድም ሶሊማን ልጆቹን ከሕንፃው ፍርስራሽ ሲከላከል ሕይወቱ አልፏል።

“በጣም አስፈሪ ነው። የሞተ ሰው አይቼ አላውቅም። ምን ማለት እንዳለበኝ አላውቅም። በጣም ፈጣን ሞት ነበር።”

ራሚ ታራዚ ደግሞ ሕንፃው በሚሳዔል ሲመታ በሥፍራው የነበረውን ሁኔታ ሲያስታውስ “ከባድ ሚሳዔል ነው። በጣም ትልቅ ከመሆኑ የተነሳ በሌላኛው ሕንፃ ውስጥ የነበሩ ሰዎች አቧሯ ለብሰው ነው የወጡት” ይላል።

የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ቤተ-ክርስቲያኑ በአቅራቢያው በነበረ የሐማስ ይዞታ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት እንደተጎዳ አምኗል። የቢቢሲ ዘገባ ነበር ።

በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ላይ የተለጠፈ ቪድዮ፣ አንድ የእስራኤል ወታደር የወደቀ ሃይማኖታዊ ሕንፃን በእብራይስጥ ቋንቋ ሲያቆሽሽ አስመልክቷል።

ቢቢሲ ለእስራኤል መከላከያ ይህን ቪድዮ ልኮ አስተያየት ቢጠይቅም ምላሽ አላገኘም።

የለንደን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የአርኪዮሎጂ ተቋም ፕሮፌሰር የሆኑት ጆርጂያ አንድሪው፣ በጋዛ ሰርጥ ጉዳት የደረሰባቸውን ሕንፃዎች ሲያጠኑ ቆይተዋል።

ፕሮፌሰሯ እኒህ ሃይማኖታዊ ሥፍራዎች በጣም ትልቅ ታሪካዊ ጠቀሜታ አላቸው ይላሉ።

“[ጥቃቱ] ሰዎች ከእነዚህ ሕንፃዎች ጋር ያላቸውን ቁርኝት ለማጥፋት እንደተደረገ ሙከራ ነው መታየት ያለበት” የሚሉት ምሑሯ መሰል ውድመት አይተው እንደማያውቁ ይናገራሉ።

በአለም ሶስተኛው ጥንታዊ ቤተክርስትያን ነው ተብሎ የሚታሰበው በዉስጡ የያዛቸውን ታሪኮቹ ቅርስና መዛግብቶችን እንደያዘ ወደ አመድነት መቀየሩን ተከትሎም ።

የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎችም ጉዳዩን በተመለከተ መግለጫ ያወጡ ሲሆን “የጋዛ ሕዝብ፣ በአያቶቻቸው ምድር ለትውልድ የኖሩ ቤተሰቦች፣ በግዞት መገደድ የለባቸውም፣ የተረፈውን ቤታቸውን፣ ቅርሶቻቸውን፣ እና የማንነታቸው መገለጫ በሆነው ምድር ላይ የመቆየት መብታቸውን ሊነጠቁ አይገባም” ሲሉ መናገራቸውን አልጀዚራ ዘገባ ያሳያል ።

የኢየሩሳሌም አብያተ ክርስቲያናት እንደ ክርስቲያን በጋዛ ሕዝብ ለሚደርስባቸው መከራ ግድየለሾች ሊሆኑ እንደማይችሉ "ወንጌል የሰውን ልጅ ሁሉ ክብር እንድንጠብቅ ያዘናልና።"
የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በጋዛ ያለውን ሰብአዊ አደጋ ለመግታት አፋጣኝ እና ቆራጥ እርምጃ እንዲወስዱ ያሳስባሉ።

የሰው ልጅ ሕይወት ቅድስና እና መከላከያ የሌላቸውን የመጠበቅ የሞራል ግዴታ ከጥፋት እና ተስፋ መቁረጥ ይበልጡ። ተስፋ የቆረጡ ሰዎች አፋጣኝ ያልተገደበ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲደረግ እንጠይቃለን።"ያሉት ኩስቶስ ብፁዕ አቡነ ፍራንቸስኮ ፓተን
"ልመናቸውን በእምነት እና በተስፋ መልእክት ሲያጠቃልሉ፣ የኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ለሐዘን መጽናናት፣ ለቆሰሉት ፈውስ እና መከራ ቢደርስባቸውም በአገራቸው ለሚቀሩት ጽናትን ለማግኘት እንደሚፀልዩ ተናግረዋል ። በማለት የዘገበው ጀሩሳሌም ፖስት ነበር ።

እነዚህና ምናልባት በዝርዝር ብፅፋቸዉ አንባቢያን እንዳይሰለቹ የተዉኳቸዉ በሁለቱም ወገኖች በሀማስና እስራኤል በተራዘመ ጦርነት ምክንያት በ365 ስኩዌር ኪሎሜትር በ40 ኪሎሜትር የባህር እርዝማኔ ክልል ዉስጥ የምትገኘውን ጋዛ ሰርጥ ይኖሩ በነበሩ ክርስትያኖች ላይ የደረሱ ግፎች ናቸው ። ከዚህ ምስቅልቅል በኋላ ለወትሮው ጥቂት የነበረው የፍልስጤማውያን ክርስትያኖች ቁጥር አሽቆልቁሎ 800 ብቻ ቀርቷል ። እነዚህም የማምለኪያ ስፍራዎች ስለወደሙባቸዉ መቀጠላቸው ያጠራጥራል ሲል ያስነበበው ደግሞ አለምአቀፋዊ የክርስቲያን ህብረት ነዉ ።

( ታዴ የማመይ ልጅ በየኔታ ትዩብ )

10 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.