Logo
YenetaTube
ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ ፖርቹጋልና ብሪታንያ ለፍልስጤም ሀገረ መንግስት እውቅና ሰጡ

ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ ፖርቹጋል እና ብሪታንያ ለፍልስጤም ሀገረ መንግስት እውቅና ሰጡ።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ሰኞ ከሚካሄደው ስብሰባ ጎን ለጎን በሳውዲ አረቢያ እና በፈረንሳይ መሪነት በርካታ ሀገራት ለፍልስጤም ሀገረ መንግስት እውቅና እንደሰጡ በመሪዎቻቸው በኩል አሳውቀዋል ሲሉ ቢቢሲ እና አልጀዚራ ዘግበዋል።

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኒ እሁድ እለት በሰጡት መግለጫ “አሁን ካናዳ ለፍልስጤም ሀገረ መንግስት እውቅና ሰጥታለች" ብለዋል።

አውስትራሊያ በበኩሏ ለፍልስጤም ግዛት ዛሬ በይፋ እውቅና ሰጥታለች።

የፖርቹጋሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ሀገራቸው ለፍልስጤም ሀገረ መንግስት እውቅና መስጠቷን ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በካቢኔያቸው ስብሰባ ላይ በሰጡት መግለጫ የፍልስጤም መንግስት መመስረት የእስራኤልን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል እና “ለሽብርተኝነት ሽልማት ነው” ብለዋል።

አክለውም "እስራኤል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በሌሎች መድረኮች ሁሉ" በሀገራቸው ላይ የሚነዙትን የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የፍልስጤም መንግስት መመስረትን የሚቃወሙ ናቸው" ሲሉ ገልፀዋል ።

Gazette Plus

9 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.