1 month ago
የሃንታ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ዓለም አቀፍ ርብርብ እየተደረገ ነው
****************
በቅርቡ በደቡብ አሜሪካ ጉዞ አድርጋ በነበረችው MV Hondius በተባለች የመዝናኛ መርከብ ላይ በተቀሰቀሰው የሃንታ ቫይረስ ወረርሽኝ፣ ከአሜሪካ እና ከፈረንሳይ የመጡ ተጓዦች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
እስከአሁን በመርከቧ ላይ የነበሩ 3 ሰዎች የሞቱ ሲሆን፣ ሁለቱ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአሜሪካ እና በፈረንሳይ የተለዩትን ጨምሮ በድምሩ 7 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ፣ ሌሎች 2 ደግሞ ተጠርጥረዋል።
በመርከቧ ላይ የነበሩ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች (እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ ስፔን እና ዩክሬን) ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በክትትል እና በገለልተኛ ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ።
የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ከመርከቧ ለወጡ ተጓዦች የ42 ቀናት የገለልተኛ ቆይታ (Isolation) እንዲደረግ ቢመክርም፣ አሜሪካ ግን ቫይረሱ እንደ ኮቪድ በፍጥነት እንደማይሰራጭ በመጥቀስ ጥብቅ ገደብ አላስቀመጠችም።
ቫይረሱ በአብዛኛው ከአይጥ ወደ ሰው የሚተላለፍ ቢሆንም፣ አሁን የተከሰተው ዝርያ (Andes strain) ግን ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ ዕድል እንዳለው የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
የአፍሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ቫይረሱ በአፍሪካ የመሰራጨት ዕድሉ ዝቅተኛ ቢሆንም፣ ሀገራት በየብስ እና በባሕር በሮች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ትኩሳት፣ ከፍተኛ ድካም፣ የጡንቻ ሕመም፣ የሆድ ሕመም፣ ማቅለሽለሽ እና የመተንፈስ ችግር ዋና ዋና ምልክቶቹ ናቸው።
ምንም እንኳን የጤና ባለሙያዎች ቫይረሱ በሰፊው የመሰራጨት ዕድሉ ዝቅተኛ ነው ቢሉም፣ ጥንቃቄው ግን ቀጥሏል።
በቢታንያ ሲሳይ
#healthnews #hantavirus #mvhondius #globalhealth
****************
በቅርቡ በደቡብ አሜሪካ ጉዞ አድርጋ በነበረችው MV Hondius በተባለች የመዝናኛ መርከብ ላይ በተቀሰቀሰው የሃንታ ቫይረስ ወረርሽኝ፣ ከአሜሪካ እና ከፈረንሳይ የመጡ ተጓዦች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
እስከአሁን በመርከቧ ላይ የነበሩ 3 ሰዎች የሞቱ ሲሆን፣ ሁለቱ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአሜሪካ እና በፈረንሳይ የተለዩትን ጨምሮ በድምሩ 7 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ፣ ሌሎች 2 ደግሞ ተጠርጥረዋል።
በመርከቧ ላይ የነበሩ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች (እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ ስፔን እና ዩክሬን) ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በክትትል እና በገለልተኛ ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ።
የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ከመርከቧ ለወጡ ተጓዦች የ42 ቀናት የገለልተኛ ቆይታ (Isolation) እንዲደረግ ቢመክርም፣ አሜሪካ ግን ቫይረሱ እንደ ኮቪድ በፍጥነት እንደማይሰራጭ በመጥቀስ ጥብቅ ገደብ አላስቀመጠችም።
ቫይረሱ በአብዛኛው ከአይጥ ወደ ሰው የሚተላለፍ ቢሆንም፣ አሁን የተከሰተው ዝርያ (Andes strain) ግን ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ ዕድል እንዳለው የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
የአፍሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ቫይረሱ በአፍሪካ የመሰራጨት ዕድሉ ዝቅተኛ ቢሆንም፣ ሀገራት በየብስ እና በባሕር በሮች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ትኩሳት፣ ከፍተኛ ድካም፣ የጡንቻ ሕመም፣ የሆድ ሕመም፣ ማቅለሽለሽ እና የመተንፈስ ችግር ዋና ዋና ምልክቶቹ ናቸው።
ምንም እንኳን የጤና ባለሙያዎች ቫይረሱ በሰፊው የመሰራጨት ዕድሉ ዝቅተኛ ነው ቢሉም፣ ጥንቃቄው ግን ቀጥሏል።
በቢታንያ ሲሳይ
#healthnews #hantavirus #mvhondius #globalhealth
1 month ago
ሀንታ ቫይረስ አዲሱ የዓለም የጤና ስጋት
#ethiopia | በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ በሚጓዝ የቱሪስት መርከብ ላይ የሀንታ ቫይረስ መገኘቱን የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ከፍተኛ ስጋት ተፈጥሯል።
እንደ አሜሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (CDC) መረጃ ከሆነ ይህ ቫይረስ በዋነኝነት የሚተላለፈው በአይጦች ሽንት፣ እዳሪ ወይም ምራቅ የተበከለ አየርን ሰዎች ወደ ውስጥ በሚተነፍሱበት ወቅት ነው።
እስካሁን ባለው መረጃ የሦስት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን ሌሎች ታማሚዎች እና ተጠርጣሪዎች በህክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ።
ቫይረሱ ከባድ የመተንፈሻ አካላት ችግር የሚያስከትል ሲሆን ከፍተኛ ትኩሳት፣ የጡንቻ ሕመም እና ሳምባ በፈሳሽ መሞላት ዋና ዋና ምልክቶቹ ናቸው።
ምንም እንኳን ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ እድሉ ዝቅተኛ ቢሆንም ድርጅቱ ጥንቃቄን ለማስቀደም ሲል ተጠርጣሪዎች ለ45 ቀናት በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ ወስኗል።
ቫይረሱ ለሞት የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ተጓዦች እና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
#hantavirus #globalhealth #who #healthalert #virusoutbreak #cdc #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ በሚጓዝ የቱሪስት መርከብ ላይ የሀንታ ቫይረስ መገኘቱን የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ከፍተኛ ስጋት ተፈጥሯል።
እንደ አሜሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (CDC) መረጃ ከሆነ ይህ ቫይረስ በዋነኝነት የሚተላለፈው በአይጦች ሽንት፣ እዳሪ ወይም ምራቅ የተበከለ አየርን ሰዎች ወደ ውስጥ በሚተነፍሱበት ወቅት ነው።
እስካሁን ባለው መረጃ የሦስት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን ሌሎች ታማሚዎች እና ተጠርጣሪዎች በህክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ።
ቫይረሱ ከባድ የመተንፈሻ አካላት ችግር የሚያስከትል ሲሆን ከፍተኛ ትኩሳት፣ የጡንቻ ሕመም እና ሳምባ በፈሳሽ መሞላት ዋና ዋና ምልክቶቹ ናቸው።
ምንም እንኳን ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ እድሉ ዝቅተኛ ቢሆንም ድርጅቱ ጥንቃቄን ለማስቀደም ሲል ተጠርጣሪዎች ለ45 ቀናት በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ ወስኗል።
ቫይረሱ ለሞት የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ተጓዦች እና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
#hantavirus #globalhealth #who #healthalert #virusoutbreak #cdc #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
ገዳይ ቫይረስ የተሸከመችው መርከብ እየገሰገሰች ነው
#ethiopia | በአደገኛው የሃንታ ቫይረስ (Hantavirus) ወረርሽኝ የተመታችው 'ኤም.ቪ ሆንዲየስ' (MV Hondius) የተሰኘችው መርከብ፣ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ሆና ወደ ስፔን የካናሪ ደሴቶች እየተቃረበች መሆኑ ተሰምቷል።
በመርከቧ ላይ በድንገት በተከሰተው በዚህ ወረርሽኝ እስካሁን የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 150 ተጓዦችም በቫይረሱ ሊያዙ ይችላሉ የሚለው ስጋት በዓለም አቀፍ የጤና ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቷል።
የሕክምና ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት፣ በመርከቧ ላይ የተከሰተው የቫይረስ ዝርያ 'አንዴስ' (Andes strain) የተሰኘው እጅግ ገዳይ ዝርያ ነው። ይህ ዝርያ ከሌሎች የሃንታ ቫይረስ አይነቶች ለየት የሚያደርገው በሰው እና በሰው መካከል የመተላለፍ ከፍተኛ አቅም ያለው መሆኑ ነው። ይህም በመርከቧ ጠባብ ክፍሎች ውስጥ ለሚገኙ ተጓዦች ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ እና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎታል።
መርከቧ ወደ የብስ ከመድረሷ በፊት የስፔን የጤና ባለሥልጣናት የካናሪ ደሴቶችን ከወረርሽኙ ለመጠበቅ ጥብቅ የኳራንቲን (የለይቶ ማቆያ) ዝግጅቶችን እያጠናቀቁ ነው። ቫይረሱ ወደ ደሴቶቹ ነዋሪዎች እንዳይሰራጭ ለማድረግ መርከቧ በባሕር ላይ እንድትቆይ ወይም በልዩ የሕክምና ክትትል እንድትገባ ለማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እየተደረገ ይገኛል።
የዓለም ጤና ድርጅትና የሚመለከታቸው አካላት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉት ሲሆን፣ በቀጣይ ሰዓታት መርከቧ ወደ ወደብ የምትገባበት ሁኔታ ይወሰናል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#mvhondius #hantavirus #spain #healthalert #andesvirus #breakingnews #globalhealth #የጤና_መረጃ #ሰበር_ዜና
#ethiopia | በአደገኛው የሃንታ ቫይረስ (Hantavirus) ወረርሽኝ የተመታችው 'ኤም.ቪ ሆንዲየስ' (MV Hondius) የተሰኘችው መርከብ፣ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ሆና ወደ ስፔን የካናሪ ደሴቶች እየተቃረበች መሆኑ ተሰምቷል።
በመርከቧ ላይ በድንገት በተከሰተው በዚህ ወረርሽኝ እስካሁን የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 150 ተጓዦችም በቫይረሱ ሊያዙ ይችላሉ የሚለው ስጋት በዓለም አቀፍ የጤና ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቷል።
የሕክምና ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት፣ በመርከቧ ላይ የተከሰተው የቫይረስ ዝርያ 'አንዴስ' (Andes strain) የተሰኘው እጅግ ገዳይ ዝርያ ነው። ይህ ዝርያ ከሌሎች የሃንታ ቫይረስ አይነቶች ለየት የሚያደርገው በሰው እና በሰው መካከል የመተላለፍ ከፍተኛ አቅም ያለው መሆኑ ነው። ይህም በመርከቧ ጠባብ ክፍሎች ውስጥ ለሚገኙ ተጓዦች ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ እና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎታል።
መርከቧ ወደ የብስ ከመድረሷ በፊት የስፔን የጤና ባለሥልጣናት የካናሪ ደሴቶችን ከወረርሽኙ ለመጠበቅ ጥብቅ የኳራንቲን (የለይቶ ማቆያ) ዝግጅቶችን እያጠናቀቁ ነው። ቫይረሱ ወደ ደሴቶቹ ነዋሪዎች እንዳይሰራጭ ለማድረግ መርከቧ በባሕር ላይ እንድትቆይ ወይም በልዩ የሕክምና ክትትል እንድትገባ ለማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እየተደረገ ይገኛል።
የዓለም ጤና ድርጅትና የሚመለከታቸው አካላት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉት ሲሆን፣ በቀጣይ ሰዓታት መርከቧ ወደ ወደብ የምትገባበት ሁኔታ ይወሰናል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#mvhondius #hantavirus #spain #healthalert #andesvirus #breakingnews #globalhealth #የጤና_መረጃ #ሰበር_ዜና
Comments