6 months ago
በሾፌር አልባው ታክሲ ውስጥ የተወለደ ህፃን
#ethiopia | ሾፌር አልባ ታክሲዎችን ለደምበኞች በማቅረብ የሚታወቀው ዋይሞ ኩባንያ አንዲት ሴት ወደ ሆስፒታል በማቅናት ሳለች በመኪና የኃለኛ ወንበር ልጅ መገላገሏን አሳውቋል።
የዋይሞ ኩባንያ ቃል አቀባይ እንደተናገሩት አገልግሎት ፈላጊዋ እንስት ሾፌር አልባ ታክሲ (ሮቦት ታክሲ) ያዘዘችው ወደ ጤና ተቋም ለመሄድ አንደነበር እና ጉዞ ሲጀምሩም በመኪናው የኃላ መቀመጫ ያልተለመደ እንቅስቅሴ በጉዞ አስተባባሪ ቡድኖች መታዘባቸውን ተከትሎ ለፖሊስ የአስቸኳይ እርዳታ ጥሪ ማስተላለፋቸውን ለኬቲቪዩ ፎክስ 2 ቻናል ተናግረዋል።
ዩፒአይ በበኩሉ እናት መኪና ውስጥ ካለ ሰው እርዳታ ልጇን በሰላም የተገላገለች ሲሆን ሰው አልባው መኪናም በመዳረሻነት ወደታዘዘው ሳንፍራንሲስኮ ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ለተጨማሪ የህክምና እርዳታ አድርሷታል።
እናት እና ልጅን ለድንገተኛ ህክምና የተረከበው የዩኒቨርስቲው የህክምና ማዕከልም እናት እና በታክሲ ውስጥ የተወለደውን አዲሱ ህፃን በመልካም ሁኔታ እንደተረከባቸው ማረጋገጫ ሰጥቷል።
#etventertainment
#ethiopia | ሾፌር አልባ ታክሲዎችን ለደምበኞች በማቅረብ የሚታወቀው ዋይሞ ኩባንያ አንዲት ሴት ወደ ሆስፒታል በማቅናት ሳለች በመኪና የኃለኛ ወንበር ልጅ መገላገሏን አሳውቋል።
የዋይሞ ኩባንያ ቃል አቀባይ እንደተናገሩት አገልግሎት ፈላጊዋ እንስት ሾፌር አልባ ታክሲ (ሮቦት ታክሲ) ያዘዘችው ወደ ጤና ተቋም ለመሄድ አንደነበር እና ጉዞ ሲጀምሩም በመኪናው የኃላ መቀመጫ ያልተለመደ እንቅስቅሴ በጉዞ አስተባባሪ ቡድኖች መታዘባቸውን ተከትሎ ለፖሊስ የአስቸኳይ እርዳታ ጥሪ ማስተላለፋቸውን ለኬቲቪዩ ፎክስ 2 ቻናል ተናግረዋል።
ዩፒአይ በበኩሉ እናት መኪና ውስጥ ካለ ሰው እርዳታ ልጇን በሰላም የተገላገለች ሲሆን ሰው አልባው መኪናም በመዳረሻነት ወደታዘዘው ሳንፍራንሲስኮ ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ለተጨማሪ የህክምና እርዳታ አድርሷታል።
እናት እና ልጅን ለድንገተኛ ህክምና የተረከበው የዩኒቨርስቲው የህክምና ማዕከልም እናት እና በታክሲ ውስጥ የተወለደውን አዲሱ ህፃን በመልካም ሁኔታ እንደተረከባቸው ማረጋገጫ ሰጥቷል።
#etventertainment
7 months ago
137 ቲሸርቶችን ደራርቦ ግማሽ ማራቶን የሮጠው ግለሰብ
#ethiopia | ዩፒአይ በዘገባው ግለሰቡን የክብረ ወሰን አዳኙ ብሎ ጠርቶታል። ይህንንም ለማድረግ ዴቪድ ራሽ በአይዳሆ ግማሽ ማራቶን ተካፍሏል።
ዴቪድ በድንቃድንቅ መዝገብ ስሙን ለማስፈር ካለው ጉጉት የተነሳ በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር 2019 አንድ መቶ አስራ አንድ ቲሸርቶችን ደራርቦ በግማሽ ማራቶን ውድድር ተሳትፏል።
የድንቃድንቅ መዝገብም 'ይሄማ አዲስ ነገር ነው' ብሎ ድርጊቱን መዘገበለት። ይሁንና ከጥቂት ዓመታት በኃላ 127 ቲሸርቶችን በደራረበው ተሳታፊ ስሙን እና ክብሩን ተነጠቀ።
ዳግም ክብሩን በስሙ ለማፃፍም ዴቪድ ከፍተኛ ልምምድ አደረገ። በ2024 ወደ አይዳሆ ፖታቶ ግማሽ ማሮቶን ዳግም በመሳተፍ 114 ቲሸርቶችን እንደለበሰ አንገቱ ተጨማሪ ልብሶችን ማጥለቅ ባለመቻሉ እና ከደም ዝውውር ጋር በተያያዘ ባጋጠመው ችግር እቅዱን ማሳካት አልቻለም ነበር።
በዚህ ዓመት ግን ዴቪድ የተነጠቀውን ክብር ዳግም አስመልሷል። በአይዳሆ ግማሽ ማራቶን ላይ ተሳትፎ 137 ቲሸርቶችን በመልበስ ውድድሩን ሲያጠናቅቅ የድንቃድንቅ መዝገብ ደግሞ አዲስ ክብረ ወሰን በማለት መዝግቦለታል።
ዴቪድ 21 ኪሎ ሜትሩን ሲያጠናቅቅ 21.77 ኪሎ ግራም የሚመዝን ቲሸርት ተሸክሞ እንደሆነ ሳማ ቲቪ ዘግቧል።
#etventertainment
#ethiopia | ዩፒአይ በዘገባው ግለሰቡን የክብረ ወሰን አዳኙ ብሎ ጠርቶታል። ይህንንም ለማድረግ ዴቪድ ራሽ በአይዳሆ ግማሽ ማራቶን ተካፍሏል።
ዴቪድ በድንቃድንቅ መዝገብ ስሙን ለማስፈር ካለው ጉጉት የተነሳ በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር 2019 አንድ መቶ አስራ አንድ ቲሸርቶችን ደራርቦ በግማሽ ማራቶን ውድድር ተሳትፏል።
የድንቃድንቅ መዝገብም 'ይሄማ አዲስ ነገር ነው' ብሎ ድርጊቱን መዘገበለት። ይሁንና ከጥቂት ዓመታት በኃላ 127 ቲሸርቶችን በደራረበው ተሳታፊ ስሙን እና ክብሩን ተነጠቀ።
ዳግም ክብሩን በስሙ ለማፃፍም ዴቪድ ከፍተኛ ልምምድ አደረገ። በ2024 ወደ አይዳሆ ፖታቶ ግማሽ ማሮቶን ዳግም በመሳተፍ 114 ቲሸርቶችን እንደለበሰ አንገቱ ተጨማሪ ልብሶችን ማጥለቅ ባለመቻሉ እና ከደም ዝውውር ጋር በተያያዘ ባጋጠመው ችግር እቅዱን ማሳካት አልቻለም ነበር።
በዚህ ዓመት ግን ዴቪድ የተነጠቀውን ክብር ዳግም አስመልሷል። በአይዳሆ ግማሽ ማራቶን ላይ ተሳትፎ 137 ቲሸርቶችን በመልበስ ውድድሩን ሲያጠናቅቅ የድንቃድንቅ መዝገብ ደግሞ አዲስ ክብረ ወሰን በማለት መዝግቦለታል።
ዴቪድ 21 ኪሎ ሜትሩን ሲያጠናቅቅ 21.77 ኪሎ ግራም የሚመዝን ቲሸርት ተሸክሞ እንደሆነ ሳማ ቲቪ ዘግቧል።
#etventertainment
Sponsored by
Surafel
Comments