5 months ago
#ቃለየሱስ በቀለ - የአቪየሽን ወርቃማው ጋዜጠኛ
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
#በዚህ የስነዳ ሥራችን ውስጥ በቅፅ 3 ከተካተቱት 20 ዘርፎች ውስጥ የሥራ ዘርፎች ውስጥ ሚድያ አንዱ ነው። በአሁኑ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች እየተሰነዱ ይገኛሉ። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
#ዛሬን ሰንደን የምናስነብባችሁ የሚድያ ባለሙያ የቃለየሱስ በቀለን የሙያ ታሪክ ነው። በሚድያው ሥራ ሩብ ክፍለ- ዘመን የዘለቀው ቃለየሱስ በአቬሽን እና ማዕድን ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመዘገብ ትልቅ አሻራ አኑሯል። በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ በአገራችን በአንድ ርዕስ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ወይም ተክኖ መዘገብ ባልተለመደበት ሁኔታ ቃለየሱስ ችሎ አሳይቷል። ከባለታሪኩ የተገኘውን መረጃ በማግኘት፣ የቅርብ ሰዎቹን በማነጋገር የሙያ ታሪኩ ተሰንዷል። ዕዝራ እጅጉ እና ታደሠ ማሞ አጠናክረውታል።
፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#ትውልድና ዕድገት
‹‹የትኛውም አውሮፕላን ወደ አየር አኮብኩቦ መነሳቱ የተለመደ የጉዞው አማራጭ ቢሆንም አውሮፕላኑ ካሰበበት ደርሶ ማረፉ ደግሞ የግድ መሆን ያለበት ተግባር ነው፡፡››የሚል የአቪየሽን አባባል አለ፡፡በዚህ አባባል ተንደርድረን ወደ ውስጥ እንዝለቅ፡፡ሁሉም ዘርፍ የየራሱ አነፍናፊ ጋዜጠኞች እንዳሉት ሁሉ ቃለየሱስ በቀለ የተባለ ህልመኛና ደፋር ጋዜጠኛ በአቪየሽኑ ዘርፍ በተለየ መንገድ የራሱን የብዕር አሻራ ማኖር መቻሉ የዚህ ፅሁፋችን መነሻ ነው፡፡
#ቃለየሱስ በቀለ የውልደቱም ሆነ የእድገቱ መነሻ የምስራቅ ሸዋ አዳማ (ናዝሬት) ከተማ ናት፡፡ሀምሌ 18/1967 ዓ.ም በአዳማ ሀይለ ማሪያም ማሞ ሆስፒታል ቃለየሱስ የተባለ ብላቴና ከተፋፋመ ምጥ ውስጥ ወቅቱ አብዮታዊ ለውጥ ኢትዮጵያን በሚንጥበት በዚያ ጊዜ የለውጥ አየሩን እየማጉ ድምፃቸውን በማሰማት ይቺን ምድር ከተቀላቀሉት ጨቅላዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቦ በስሙ የልደት ካርድ ወጣለት፡፡
#ይህ ሰው ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ያለውን የትምህርት ጉዞውን ያሳለፈው በናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ነው፡፡ትምህርት ቤቱ ከቀለም ትምህርት በተጨማሪ ተማሪዎችን በግብረ ገብና በመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት አንፆ በማብቃት ረገድ የተዋጣለት እንደነበር ቃለየሱስና አብረውት የተማሩት ሁሉ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው፡፡
#በ1986 ዓ.ም ውጤታማ ሆኖ የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅን ደጃፍ መርገጥ የቻለው ቃለየሱስ በኮሌጁ ሁለት ዓመታት በአካውንቲነግ ሙያ ተምሮ ቢያሳልፍም የሂሳብ ባለሙያ ሆኖ መቀጠሉ ስላልተዋጣልኝ ከልጅነቴ ጀምሮ አልመውና እፈልገው የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ ለመቀላቀል መንከራተት የየዕለት ተግባሬ ሆነ ይላል፡፡ያኔምደፋር ብዕሩን ስሎ አሰሳውን የጀመረውና በእንግሊዝኛ ቋንቋ አርቲክሎችን እየዘጋጀ ለዴይሊ-ሞኒተር እና ዘ-ሪፖርተር ጋዜጦች ማቅረብ መጀመሩ የምኞት ጭላንጭሉን ወገግ አደረገለት፡፡
#ጋዜጠኝነት
እንደምኞትና ፍላጎቱም መንከራተቱ ፍሬ አፍርቶ ሳምንታዊ የቢዝነስ ጋዜጣ በሆነው ፎርቹን ጋዜጣ ላይ በሪፖርተርነት ተቀጥሮ ማገልገል ጀመረ፡፡ምኞትና ህልሙ መሬት እንዲረግጡ ቀዳሚውን ዕድል ያመቻቸለት የፎርቹን ጋዜጣ መስራችና ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው አቶ ታምራት ሀይለ ጊዮርጊስ በቃለየሱስ የህይወት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡የጋዜጠኝነት ሀ ሁን ከማስቆጠር ጀምሮ ከዚያም ባሻገር አንደ ዓለም ባንክ፣የአሜሪካ ኤምባሲና ብሪቲሽ ካውንስል ያሉ ተቋማት በሚያዘጋጁት የሚዲያ ስልጠናዎች ላይ ተሳታፊ እንድሆን ዕድሉን ከማመቻቸት አልፎ ጠንካራ የጋዜጠኝነት ሰብዕናን እንድላበስ ያደረገኝ ባለውለታዬ ታምራት ነው ይላል ቃለየሱስ፡፡
#ወትሮም ለጋዜጠኝነት ታላቅ ጉጉት የነበረው ቃለየሱስ ዜና እንዴት ይፃፋል፣የዜና ግብዓቶች እንዴት ይሰበሰባሉ፣የዜና አስተማማኝ ምንጮችን እንዴት ማዳበር ይቻላል፣ፊቸር አርቲክል እንዴት ይፃፋል የሚሉና ሌሎችም ስልጠናዎችን አግኝቶ በብዕሩ መጠንከር የቻለው በፎርቹን ጋዜጣ ቆይታው እንደሆነ ያስታውሳል፡፡መች ይሄ ብቻ ከሀገር ውጪም በዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት በኤር ባስ አማካኝነት ከበረራና የበረራ ደህንነት መረጃ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ስልጠናዎችን በስፋት በመውሰድ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬቶችን ተቀብሏል፡፡
#ቃለየሱስ ባለውለታዎቼ ብዙ ናቸው ይላል፡፡የፎርቹን ጋዜጣ ኤዲተር የነበሩት መላኩ ደምሴና ይበቃል ጌታሁን በጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ኮትኩተው ለውጤት አብቅተውኛል ካለ በኋላ በአጠቃላይ የፎርቹን ኤዲተሮች እኔን ጠፍጥፈው ሠርተውኛል ብል ማጋነን አይሆንም በሚል ያለፈበትን የጋዜጠኝነት ህይወት በአጭሩ ገልፆታል፡፡
#ከፎርቹን የሁለት ዓመታት ቆይታ በኋላ ሪፖርተር ጋዜጣን በመቀላቀል ለ18 ዓመታት ከከፍተኛ ሪፖርተርነት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለው ቃለየሱስ ከሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ጋር መሥራት መታደል ነው ይላል፡፡ከአቶ አማረ ጋዜጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአገር ፍቅርና ብሔራዊ ጥቅምን (National Interest)፣ደግነትንና ለሠራተኞቹ ያለውን ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ለጋዜጠኞች የሙያ ነፃነት ሰጥቶ ሠርቶ የሚያሠራበትን መልካም ትምህርት ቀስሜያለሁ ብሏል፡፡በሪፖርተር ሳለሁም በርካታ የሙያ ማሻሻያዎችንና የአጭር ጊዜ ሥልጠናዎችን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገሮች አግኝቻለሁ በማለት ትናንቱን ያመሰግናል፡፡
#በዘ -ሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ የማቀርባቸው ዘገባዎቼ በአብዛኛው ቢዝነስ ተኮር ነበሩ የሚለው ቃለየሱስ በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድን ዘርፎች ላይ አተኩር ስለነበር፤በእነዚህ ዙሪያ በሚሠሩ የውጭ መጽሔቶች ለእኛም ጻፍልን የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ ኤርላይን ፍሊት ማኔጅመንት፣ወርልድ ኤር ኒውስ፣ኤርላይን ኢኮኖሚክስ፣አፍሪካን ኤሮስፔስና ዓረቢያን ኤሮስፔስ፣አቪዬሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ፣አፍሪካን ቢዝነስ እና አፍሪካን ማይኒንግ ጆርናል ለተባሉ መጽሔቶች በፍሪላንስነት ለረዥም ዓመታት ሠርቻለሁ ይላል፡፡
እ.ኤ.አ.በ2008 በእንግሊዝ አገር በሚካሄድ “Best Aerospace Journalist of the Year” ሽልማት ታጭቼና ለንደን ተጋብዤ ዋናውን ሽልማት ባላሸንፍም፣"How Safe Are African Airlines?" በሚል ርዕስ በኤርላይን ፍሊት መጽሔት ላይ ያሳተምኩት ጽሑፍ ከ500 ለውድድር ከቀረቡ ጽሑፎች አምስቱ ምርጥ ውስጥ ለመግባት በመቻሉ፣ሰርተፊኬት ተበርክቶልኛል ብሏል፡፡
#በ2007 ዓ.ም. በትግራይ ሽመልባ የኤርትራ ስደተኞች መጠለያ ካምፕ ጉብኝት በማድረግ፣ ስለኤርትራዊያን ስደተኞች አሳዛኝ ሕይወት "The Woes of Eritrean Refugees” በሚል ርዕስ በዘ- ሪፖርተር ጋዜጣ ያሳተምኩት ሰፊ ጽሑፍ ጄኔቭ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) ዋና መሥሪያ ቤት ተመርጦ፣ለረዥም ጊዜ በድረ ገጻቸው ላይ ለንባብ ተቀምጦ ነበር፡፡በሻሸመኔ መልካ ኦዳ ስለሚገኙ የራስ ተፈሪያን ማኅበረሰቦች በቦታው ተገኝቼ የሠራሁት "The Plight of Rastafarians in Ethiopia" ዘገባ ከራስ ተፈሪያን ማኅረሰብ ምሥጋናና ዕውቅና አስገኝቶልኛል ይላል፡፡
ቃለየሱስን አንባቢያን የሚያውቁት ስለኢትዮጵያ አየር መንገድና በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ስለሚካሄዱ የማዕድንና የነዳጅ ፍለጋዎች ተከታታይ በርካታ ዜናዎችን በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በመሥራቱ ነው፡፡ ከዚያ ባለፈም ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ጋር የመሥራት ዕድሉን አግኝቷል፡፡
#የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ለሥራ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅትም እነሱን በማገዝ የተለያዩ ሥራዎችን ከውኗል፡፡ከእነዚህም መካከል “CNN, Aljazeera, SKY News, The Economics, National Geographic, Los Angeles Times, News Week, New York Times, Christian Science Monitor, Chicago Tribune…” እና ሌሎችም ከተሳተፈባቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡
እ.ኤ.አ. በ2019 አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን በተመለከተ ሲኤንኤን (CNN) በሠራቸው ዘገባዎች ላይ በረዳት ፕሮዲዩሰርነት የሠራ ሲሆን፣በወቅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከሲኤንኤን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ምሥጋና ተችሮታል፡፡በዘገባዎቹ ላይም ሙሉ ስሙን በማስፈር ተገቢውን ዕውቅና ሰጥተውታል፡፡የአሜሪካው አልጄዚራ ኢንግሊሽ ቡድን ስለአውሮፕላን አደጋው ዶክመንተሪ ለማዘጋጀት አደጋው ከደረሰ ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅትም፣አብሮ የአገር ውስጥ ፕሮዲዩሰር (Local Producer) ሆኖ ሠርቷል፡፡
መቼ ይሄ ብቻ ቃለየሱስ የ”Fault Lines” ፕሮግራም አዘጋጅ ከሆነው ጆሽ ረሺንግ (Josh Rushing) እና ፕሮዲዩሰሯ ካቢታ ቺኩሩ ጋር የሠሩት ዶክመንተሪ የተለያዩ አህጉሮችን የሸፈነ ሲሆን፣ለኤሚ አዋርድ ዕጩ ሆኖ ቀርቦም ነበር፡፡
#ከ18 ዓመታት አገልግሎት በኃላ እ.ኤ.አ. በ2020 ሪፖርተር ጋዜጣን ተሰናብቶ ኦሪጅንስ ሚዲያን በማቌቋምና ከኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት በመውሰድ፣‹‹ኢትዮ የንግድና የኢንቨስትመንት መድረክ››የተሰኘ ፕሮግራም በሳምንት ለሁለት ቀናት እያዘጋጀ ለሦስት ዓመታት ያህል አቅርቧል፡፡ኦሪጅንስ የሚል የጉዞ (Travel Magazine) ለማሳተም እየንቀሳቀሰ የነበረ ቢሆንም፣በኮቪድ ወረርሽኝና በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለፍሬ ሊበቃለት እንዳልቻለ በቁጭት ያስታውሳል፡፡
#ገጠመኞቹ
#ቃለየሱስ በጋዜጠኝነት ሙያ የገጠሙኝ ፈተናዎች ብዙ ናቸው ይላል፡፡ሙያው ራሱ የሚያስደስት ነገር እንዳለው ሁሉ ብዙ የሚያስጨንቁና የሚከብዱ ነገሮችም አሉት።ጋዜጠኛው ከህሊናው ጋር ተሟግቶና ሚዛኑን ጠብቆ የሚሰራው ነገር አንዱ ሲሆን።ዘገባን ወቅት ጠብቆ መስራትም የራሱ ፈተና አለው። ሚዛናዊነቱ ሳይጓደልም እንኳን ስለአንድ ነገር ሲፃፍ ወይም ሲዘገብ በዜናው ምከንያት የሚጠቀሙ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ።
ወዲህ ደግሞ ጉዳቱም የዛን ያህል ነው።አንድ ሚዲያ በሚሰራው ዘገባ ባለስልጣንም ሆነ ካምፖኒ ሊሆን ይችላል የነበረውን አቅም ሊያጣ ይችላል።ይህ የሚዲያ ባህሪ ነው።ፈተናዎቹ የበዙ ቢሆኑም ጋዜጠኛው ሲፅፍ ሚዛናዊነት የተለበሰ መሆን አለበት ባይ ነው ቃለየሱስ።
#ቃለየሱስ ረጅም ዓመት የሠራው ህትመት ሚዲያ ላይ ነው።በአንድ ወቅት ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛ ጋር ወደ ትግራይ በማቅናት በኢትዮ ኤርትራ ስላለው ሁኔታ ለመዘገብ አመሩ፡፡ሽሬ አካባቢ ሽመልባ የሚባል የኤርትራ ስደተኞች ያሉበትን ስፍራ ጎብኝተውና አነጋግረዋቸው ወደ ሽራሮ ሄዱ፡፡የጦርነቱ ከተማ ወደነበረችው ባድመ ሄደውም ነዋሪዎችን፣አርሶ አደሮችና የከተማውን አስተዳደር ቃኝተውና ቃለመጠይቅ አድርገው ወደ ኤርትራ ድንበር ተጠጉ፡፡
#የኤርትራን መሬት ከወንዝ ባሻገር እያዩና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ሲያስጎበኟቸው የተቀበሩ ፈንጂዎች ስለነበሩ በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሀይል አማካኝነት የፈንጂ ማስወገድ ስራው እየተሰራ ስለነበር የምንረግጠውን መንገድ ጠቆሙን ካለ በኋላ ቀይ ቀይ የተደረገባቸውን ድንጋዮች አሳይተውን ለእግር ፉካ የምትሆን ድንጋይ አሳዩን።ቀይ ምልክት የተደረገባቸውን ድንጋዮች ትተን ሌላ ከረገጥን ልንሞት እንደምንችል ነገሩን።በፈንጂ መሀከል በጭንቅና በዝግታ ያሳለፍንውን ምንጊዜም አልረሳውም ይላል ቃለየሱስ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ በአቬየሽን፣በነዳጅ እና ማዕድን ፍለጋ ስራዎች ዙሪያ ለመዘገብ ወደ ሱማሌ ክልል ይሄዳል፡፡ከኦጋዴን ነፃ አውጪ ጋር የነበሩ ውጊያዎች ስለነበሩ አንድ ጊዜ አቦሌ ከሚባል በደቡብ ምዕራብ በሚገኝ ኩባንያ የነዳጅ ስራ ፍለጋ በሚያደረግ ካምፕ ላይ ታጣቂዎቹ ጥቃት ሰንዝረው 9 ቻይናውያን እና ወደ 65 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ህይወት ያልፋል።
ያንን ለመዘገብ ወደ አካባቢው የሄደው ቃለየሱስ ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛው ፖልስ አሎቤ ጋር ያለ እንቅልፍ ረጅም ቀናት በማሳለፋቸው በሀሩራማው ኦጋዴን ውስጥ ለረጅም ሰአታት ራሱን ስቶ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና የነቃበትን ጊዜም ያስታውሳል።ቃለየሱስ ገጠመኞቹ የትየለሌ ናቸው፡፡በችሎት ዘገባ እንዲሁም ጋምቤላ ለዘገባ ሄዶ ያጋጠሙትንም ሁሌ እያስታወሰ ይገረምባቸዋል፡፡ በተለያዩ የአቪዬሽን ስብሰባዎችና እንዲሁም በአውሮፕላን አምራች ካምፓኒዎች በአካል እየተገኘም የሚያማልሉ ዘገባዎችን አስነብቧል፡፡
#ስለ ቃለየሱስ የታላላቅ ሰዎች ምስክርነቶች
"ቃለ ኢየሱስ በቀለ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በትጋት ከሠሩ ባለሙያዎች አንዱ ነው።" ይላል የሪፖርተር ጋዜጣ መስራች አማረ አረጋዊ። ምስክርነቱንም በመቀጠል፦
"... ቃለ ኢየሱስ በአቬሽን እና በማዕድን ዘገባዎች ላይ ያተኩር እንጁ የተሰጠውን ደስ ብሎት የሚሠራ ጋዜጠኛ ነው። የጋዜጠኝነት የሥነ ምግባር ደንብን አውቆ የሚተገብር ባለሙያ ነው። ፕሮፌሽናሊዝም እንዲሰፍን የሚታገል ጠንቃቃ ባለሙያ መሆኑን መመስከር እወዳለሁ።" በማለት ገልጿል
፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#የአቶ ግርማ ዋቄ ምስክርነት
#ቃለ ኢየሱስ በቀለን ረጅም ጊዜ አውቀዋለሁ። ለአቬሽን የተለየ ፍቅር አለው። አለምአቀፍ ኮንፈረንሶች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋል። ከዚያም በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ፅሁፍ ያቀርባል።ብስለቱ ይደንቃል። ከሌሎች የስሚ ስሚ ሰምቶ ሳይሆን አንድን ጉዳይ ከስር ከመሠረቱ አውቆ የመዘገብ ችሎታውን አደንቅለታለሁ። ስለ አፍሪካ አየር መንገድ ፣ ስለ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በወጉ ተረድቶ ስለሚፅፍም ፅሑፉ ተነባቢ ለመሆን ችሏል። ኢትዮጵያ ውስጥ አቬሽን ጋዜጠኝነት በጥልቀት ሲሠሪ የማውቀው እርሱን ነው።ሌሎችም አሉ። እርሱ ግን ከፍ አድርጎ በልህቀት የሚሠራ በመሆኑ ይለያል።
ገና አየር መንገድ ሲመጣ መረጃ ለማግኘት ፍላጎት ያሳያል። ዕውነትን ለማግኘት ይጎለጉላል። አፍሪካም ውስጥ ፈጠን ብሎ አቬሽን ጋዜጠኝነት ላይ የገባ በመሆኑ ይህም ግንባር ቀደም ያደርገዋል። ቃለኢየሱስ ካለበት ካናዳ ሆኖ የአቬሽን ጋዜጠኝነትን ሙያ እንዲያሳድግ ምክሬን እለግሰዋለሁ።
አቶ ግርማ ዋቄ
የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
‹‹እኔ ቃለየሱስ በቀለን የማውቀው ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ፎርቹን ጋዜጣ አብረን ስንሠራ ጀምሮ ነው›› የሚለው የሪፖርተር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው መላኩ ደምሴ ነው፡፡‹‹ከዚያም በኌላ ለ18 ዓመታት አብረን በሪፖርተር ጋዜጣ ሠርተናል፡፡ከጀማሪ ሪፖርተርነት አንስቶ እስከ አርታኢነት በዘለቀው የሥራ ጉዞው በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድናት ዘርፍ እጅግ በጣም በርካታ ዘገባዎችን የሠራ ሲሆን፣በሁሉም ሥራዎቹ አንጀት አርስ የሚባል ጋዜጠኛ ነው፡፡ጋዜጠኝነትን ከልቡ ከማፍቀሩ የተነሳ አብረው ለሚሠሩ ጋዜጠኞች ጭምር የሙያውን ፍቅር የማጋባት ችሎታ ያለው ነው፡፡ቃለየሱስ ዘገባዎችን ሲሠራ የሁሉንም ባለጉዳዮች ደምፅ ከማካተት በተጨማሪ፣አንባቢያን ለርዕሰ ጉዳዩ ቅርበት እንዲፈጥሩ የሚያስችል ስሜትን የተካነ ነው፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በአቪዬሽን ዘገባ በግንባር ቀደምነትነት የሚጠቀስ ጋዜጠኛ ማነው ቢባል በመጀመሪያው ረድፍ ላይ የሚገኘው ቃለየሱስ ነው፡፡በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያዎችን፣አየር መንገዶችን፣በአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሳይቀር በተለያዩ አገሮች በማግኘት በሪፖርቶቹ ውስጥ ድምፃቸውን ከማካተቱም በላይ በቃለ ምልልስ ጭምር ለአንባቢያን ተደራሽ በማድረግም ወደር የለውም፡፡የአውሮፕላን አደጋዎች ሲያጋጥሙም ሆነ የተለዩ ክስተቶች ሲኖሩ ከሚሠራቸው ዘገባዎች በተጨማሪ፣በተለያዩ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማብራሪያ የሚፈለገው ቃለየሱስ ነው፡፡በውጭ ለሚዘጋጁና ቁጥራቸው ቀላል ለማይባል የአቪዬሽን መጽሔቶች በርካታ ዘገባዎችን በመሥራትም ታዋቂ ነው፡፡
‹‹በማዕድናት ዘርፍም ከካሉብ ነዳጅ የጀመረው የጋዜጠኝነት ህይወቱ በተለያዩ ክልሎች የሚደረጉ የነዳጅ፣የወርቅ፣የብረት፣የፖታሽ፣የታንታለም፣የኦፓልና ሌሎች የከበሩ ማዕድናት ፍለጋ ሥራዎችን በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታዎች፣በጂኦ ተርማል ፕሮጀክቶች፣ በፀሐይና በንፋስ ኃይል ማመንጫዎች፣በሲሚንቶና በሌሎች የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም ሰፋፊ ዘገባዎችን በማበርከት ስመጥር ሆኖ ዘልቌል፡፡በፖለቲካው መስክ ደግሞ በተለያዩ አገራዊ ምርጫዎች ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎች ተሰማርቶ አመርቂ ሪፖርቶችን በማቅረብ ችሎታውን ማስመስከር የቻለ ነው፡፡ከሪፖርተር በገዛ ፈቃዱ ከተሰናበተ በኃላም በኤፍኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት ወስዶ ያቀርባቸው የነበሩ የቢዝነስ ፕሮግራሞቹ፣የቃለየሱስን ችሎታ ከጋዜጣ አንባቢያን ወደ ሬዲዮ አድማጮች በማዝለቅ ረገድ ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ነበሩ፡፡
‹‹ቃለየሱስ ግልጽ፣ ቅን፣ ሰብዓዊነትን የሚያስቀድም፣ኃላፊነት የሚሰማው፣ በአስገራሚ ትውስታው የረሳናቸውን ጉዳዮች የማስታወስ ችሎታ ያለው፣በቀልድም ሆነ በቁምነገር የሚታወቅ፣ ከማንኛውም ሰው ጋር ወዳጅነት ለመፍጠር ምንጊዜም ዝግጁ የሆነ፣በተለይ በሪፖርተር የሥራ ባልደረቦቹ ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ምሥጉን ጋዜጠኛ ነው፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው ሰፊና ጥልቅ ትንተናዎቹ የሚታወቅ ሲሆን፣ብዙዎችም በዚህ መጠን ለነገሮች ትኩረት ሰጥቶ የማስረዳት ብቃቱን በአድናቆት የሚመሰክሩለት ነው፡፡እኔም ከሁለት አሠርት ዓመታት በላይ አብሬው ስለሠራሁ ችሎታውን በዚህ መጠን ስገልጽ በከፍተኛ ስሜት ሲሆን፣ይህንን ከመሰለ ብርቱና ታታሪ ጋዜጠኛ ጋር የመሥራት ዕድል በማግኘቴ በእጅጉ ደስተኛ ነኝ›› በማለት መላኩ ምስክርነቱን አጠቃሏል፡፡
ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው ስለ ቃለየሱስ በሰጡት ምሥክርነት ‹‹እኔ እሱን ለአየር መንገዱ ልዩ እንደ ሆነ ሰው አየዋለሁ።በጣም ትሁት፣አዳማጭ የሆነ ሰው ነው።ከየት እንዳመጣው ባላውቅም ልዩ የሆነ የኢንግሊዘኛ ፀሀፊ ነበር።በሁለት ምክንያት የሱን ፅሁፍ አነብ ነበር፡፡አንዱ በፅሁፉ ለመደሰትና እንደ ግጥም ስለምወደው ነው።ሌላው ከእውቀቱ ወይም አንብቦም ይሁን ባላውቅም የፅሁፎቹ ይዘት በሚያውቀው ነገር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው።በዚህም በጣም አበረታታዋለሁ።
‹‹ከተዋወቅን 15 ዓመታት ሆኖናል።በውጪ ህትመቶች ላይ የሚያወጣቸው ስራዎች ቃለየሱስ ብሎ ስሙ ይገለፅ ይሆናል እንጂ ማንም ነጭ የሚፅፈው አይነት ፅሁፍ ነው።የፅሁፉ ይዘትና አያያዝ ደረጃውን የጠበቀ ነው።የሚፅፍባቸው መፅሄቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ትላልቅ ናቸው።ነገር ግን ደረጃቸውን ጠብቀዋል የሚባሉትም አንዳንዴ ትርኪምርኪ ሲፅፉም ይታያል።ግን የሱ ፅሁፍ በጣም የሚያኮራ ነው።ሌላው ዜግነቱን የሚወድ ሰው ነው።ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለኢትዮጵያ አየርመንገድ በቦታው ካሉት ህዝብ ግንኙነቶች እሱ ብዙ የሰራ ይመስለኛል።እውቅናና ሽልማት ሊሰጠው በርታ ሊባል የሚገባው ልጅ ነው።ወገቡን ይዞ ነበር ለአየር መንገዱ ይሰራ የነበረው።አሁንም ቢሆን ባለበት ሆኖ ለአየርመንገዱ ነገሮችን መስመር የሚያሲዝ ሰው ነው››ብለዋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨
የቀድሞ የሲቪል አቬሽን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወሰንየለህ ሁነኛው በበኩላቸው ‹‹ከተዋወቅን ከ7 ዓመት በላይ ይሆነናል።እኔ ከማቃቸው የሚዲያ ሰዎች በጋዜጠኝነት የሱን ያህል ብዙም አቬሽን ዘርፉ ላይ ገብቶ እያንዳንዱን ነገር አይቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይሁን የግል ኦፕሬተሮቹም ጋር እንደሱ የሚፅፍ አላየሁም።እሱ ነው የተሻለ ጠይቆ አንብቦ ተረድቶ አስተዋጽዖ ለማድረግ የሚጥረው።በዛ ወቅት ቃለ እየሱስ ጥሩ ዘጋቢ ነበር።ብዙ መፅሄቶች ላይ ይሳተፋል አንዳንድ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ላይ ይሄዳል። በኢትዮጵያ አየርመንገድና በሲቪል አቬየሽን ላይ የተለየ እውቀት ያለው ነው።ምክንያቱም በየእለቱ ስለሚከታተል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አቬየሽን ኢንዱስትሪ በደንብ ያውቀው ነበርና ነው።
‹‹አቬየሽን ኢንዱስትሪው በእነዚህ መፅሄቶች በብዙ መንገድ ይጠቀማል።ህብረተሰቡ አቬየሽኑም ሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራሱን ከማስተዋወቁ በላይ ምን ላይ እንዳለ እና በተለየ አካል እንዲሰራለት ትክክለኛነቱን ይረጋገጣል።እንዲሁም ምን ያህል የግል ኦፕሬተሮች ምን ያህል በኢኮኖሚው ይሳተፋሉ የሚለውንም ለህብረተሰቡም ለመንግስትም መረጃ ይሰጣል።ስራዎቹ ለብዙ ነገሮች የመረጃ ምንጮች ሆነው ያገለግላሉ ።
‹‹ቃለእየሱስ በዚያ ወቅት የሚያደርገው የኢትዮጵያን አቬየሽን ኢንዱስትሪ ከሌላው እያነፃፀረ በሚያውቀው ልክ ለህብረተሰቡ ሙሉ መረጃ ይሰጣል።ለግል ኦፕሬተሮችም ለኢትዮጵያ አየር መንገድም ግብዐት የሚሆኑ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል።በተዘዋዋሪም ያስተዋውቃል።እውነተኛ መረጃ ሲያቀርብ ሰው ስለ አቬየሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እውቀት ያዳብራል።አብዛኛው ሰው ስለ ግል ኦፕሬተር አያውቅም አውሮፕላን አላቸው ወይ ? ብሎ የሚጠይቅም ብዙ ሰው ነው።በዚህ ጉዳይ ላይ በብዛት የሚሰራው ቃለእየሱስ ነበር››ብለዋል፡፡
‹‹በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ የቃለየሱስ አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።››ብለው ምስክርነታቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፡፡‹‹ቃለየሱስና እኔ ለረጅም ጊዜ እንተዋወቃለን በ«Reporter» ጋዜጣ ሲሰራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜናዎችንና እድገቶችን ይዘግብ ነበር።በቀጣይ የአቪዬሽን ዘርፍ ላይ ጥልቅ ፍላጎት አሳየ፤እኛም ከIATA ጋር እንዲገናኝ አደረግነው፣በተለይም በየዓመቱ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚካሄዱ የIATA አመታዊ አጠቃላይ ጉባኤዎች (AGM) ላይ የፕሬስ ኮንፈረንሶች ላይ ይሳተፍ ነበር።
‹‹በአፍሪካ አየር እና አቪየሽን (African Aerospace and Aviation) መጽሔት እና በሌሎች ከአቪየሽን ጋር የተያያዙ መጽሔቶች ላይ ጽሁፎችን ይጽፍ ነበር።በአጋርነትም ብዙ ፕሮጀክቶችን አከናውነናል። እኔም የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድ ሊቀመንበር በነበርኩበት ሰዓት፣የራሱን የጉዞና ቱሪዝም መጽሔት እንዲጀምር ወይም እንዲያስብበት ሀሣብ አቀርብለት ነበር፤እርሱም ይህን ሀሳብ በአዎንታ ይመልከተው ነበር።
‹‹በአጠቃላይ፣ ይህ ዘርፍ እስከዛሬም በቂ የሚዲያ ሽፋንና የማስተዋወቂያ መድረክ ስላልነበረው፣ ቃለየሱስ ይህን ክፍተት ልብ ብሎ በማጤን በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል።በእኔ አመለካከት፣ያበረከተው አስተዋፅኦ አስደናቂ ነው፣ለሥራውም እውቅናና ምስጋና ሊቀርብለት ይገባል››ብለዋል፡፡
ሲጠቃለል ከ15 አመት በላይ በአለም አቀፍ የአቪየሽን ስብሰባዎችን በአሜሪካ፣አውሮፓ፣አፍሪካ፣ መካከሉኛው ምስራቅ እና ኤሽያ ተሳትፌያለሁ 36 ሃገሮችንም የማየት እድል ገጥሞኛል የሚለው የአቪየሺን ባለወርቃማ ብዕሩ ቃለየሱስ በቀለ እ.ኤ.አ.ከ2023 መጨረሻ ጀምሮ ኑሮውን በካናዳ ያደረገ ሲሆን፤ለአፍሪካ ኤሮስፔስና አቪየሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ በፍሪላንስነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
#በዚህ የስነዳ ሥራችን ውስጥ በቅፅ 3 ከተካተቱት 20 ዘርፎች ውስጥ የሥራ ዘርፎች ውስጥ ሚድያ አንዱ ነው። በአሁኑ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች እየተሰነዱ ይገኛሉ። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
#ዛሬን ሰንደን የምናስነብባችሁ የሚድያ ባለሙያ የቃለየሱስ በቀለን የሙያ ታሪክ ነው። በሚድያው ሥራ ሩብ ክፍለ- ዘመን የዘለቀው ቃለየሱስ በአቬሽን እና ማዕድን ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመዘገብ ትልቅ አሻራ አኑሯል። በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ በአገራችን በአንድ ርዕስ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ወይም ተክኖ መዘገብ ባልተለመደበት ሁኔታ ቃለየሱስ ችሎ አሳይቷል። ከባለታሪኩ የተገኘውን መረጃ በማግኘት፣ የቅርብ ሰዎቹን በማነጋገር የሙያ ታሪኩ ተሰንዷል። ዕዝራ እጅጉ እና ታደሠ ማሞ አጠናክረውታል።
፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#ትውልድና ዕድገት
‹‹የትኛውም አውሮፕላን ወደ አየር አኮብኩቦ መነሳቱ የተለመደ የጉዞው አማራጭ ቢሆንም አውሮፕላኑ ካሰበበት ደርሶ ማረፉ ደግሞ የግድ መሆን ያለበት ተግባር ነው፡፡››የሚል የአቪየሽን አባባል አለ፡፡በዚህ አባባል ተንደርድረን ወደ ውስጥ እንዝለቅ፡፡ሁሉም ዘርፍ የየራሱ አነፍናፊ ጋዜጠኞች እንዳሉት ሁሉ ቃለየሱስ በቀለ የተባለ ህልመኛና ደፋር ጋዜጠኛ በአቪየሽኑ ዘርፍ በተለየ መንገድ የራሱን የብዕር አሻራ ማኖር መቻሉ የዚህ ፅሁፋችን መነሻ ነው፡፡
#ቃለየሱስ በቀለ የውልደቱም ሆነ የእድገቱ መነሻ የምስራቅ ሸዋ አዳማ (ናዝሬት) ከተማ ናት፡፡ሀምሌ 18/1967 ዓ.ም በአዳማ ሀይለ ማሪያም ማሞ ሆስፒታል ቃለየሱስ የተባለ ብላቴና ከተፋፋመ ምጥ ውስጥ ወቅቱ አብዮታዊ ለውጥ ኢትዮጵያን በሚንጥበት በዚያ ጊዜ የለውጥ አየሩን እየማጉ ድምፃቸውን በማሰማት ይቺን ምድር ከተቀላቀሉት ጨቅላዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቦ በስሙ የልደት ካርድ ወጣለት፡፡
#ይህ ሰው ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ያለውን የትምህርት ጉዞውን ያሳለፈው በናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ነው፡፡ትምህርት ቤቱ ከቀለም ትምህርት በተጨማሪ ተማሪዎችን በግብረ ገብና በመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት አንፆ በማብቃት ረገድ የተዋጣለት እንደነበር ቃለየሱስና አብረውት የተማሩት ሁሉ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው፡፡
#በ1986 ዓ.ም ውጤታማ ሆኖ የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅን ደጃፍ መርገጥ የቻለው ቃለየሱስ በኮሌጁ ሁለት ዓመታት በአካውንቲነግ ሙያ ተምሮ ቢያሳልፍም የሂሳብ ባለሙያ ሆኖ መቀጠሉ ስላልተዋጣልኝ ከልጅነቴ ጀምሮ አልመውና እፈልገው የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ ለመቀላቀል መንከራተት የየዕለት ተግባሬ ሆነ ይላል፡፡ያኔምደፋር ብዕሩን ስሎ አሰሳውን የጀመረውና በእንግሊዝኛ ቋንቋ አርቲክሎችን እየዘጋጀ ለዴይሊ-ሞኒተር እና ዘ-ሪፖርተር ጋዜጦች ማቅረብ መጀመሩ የምኞት ጭላንጭሉን ወገግ አደረገለት፡፡
#ጋዜጠኝነት
እንደምኞትና ፍላጎቱም መንከራተቱ ፍሬ አፍርቶ ሳምንታዊ የቢዝነስ ጋዜጣ በሆነው ፎርቹን ጋዜጣ ላይ በሪፖርተርነት ተቀጥሮ ማገልገል ጀመረ፡፡ምኞትና ህልሙ መሬት እንዲረግጡ ቀዳሚውን ዕድል ያመቻቸለት የፎርቹን ጋዜጣ መስራችና ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው አቶ ታምራት ሀይለ ጊዮርጊስ በቃለየሱስ የህይወት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡የጋዜጠኝነት ሀ ሁን ከማስቆጠር ጀምሮ ከዚያም ባሻገር አንደ ዓለም ባንክ፣የአሜሪካ ኤምባሲና ብሪቲሽ ካውንስል ያሉ ተቋማት በሚያዘጋጁት የሚዲያ ስልጠናዎች ላይ ተሳታፊ እንድሆን ዕድሉን ከማመቻቸት አልፎ ጠንካራ የጋዜጠኝነት ሰብዕናን እንድላበስ ያደረገኝ ባለውለታዬ ታምራት ነው ይላል ቃለየሱስ፡፡
#ወትሮም ለጋዜጠኝነት ታላቅ ጉጉት የነበረው ቃለየሱስ ዜና እንዴት ይፃፋል፣የዜና ግብዓቶች እንዴት ይሰበሰባሉ፣የዜና አስተማማኝ ምንጮችን እንዴት ማዳበር ይቻላል፣ፊቸር አርቲክል እንዴት ይፃፋል የሚሉና ሌሎችም ስልጠናዎችን አግኝቶ በብዕሩ መጠንከር የቻለው በፎርቹን ጋዜጣ ቆይታው እንደሆነ ያስታውሳል፡፡መች ይሄ ብቻ ከሀገር ውጪም በዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት በኤር ባስ አማካኝነት ከበረራና የበረራ ደህንነት መረጃ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ስልጠናዎችን በስፋት በመውሰድ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬቶችን ተቀብሏል፡፡
#ቃለየሱስ ባለውለታዎቼ ብዙ ናቸው ይላል፡፡የፎርቹን ጋዜጣ ኤዲተር የነበሩት መላኩ ደምሴና ይበቃል ጌታሁን በጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ኮትኩተው ለውጤት አብቅተውኛል ካለ በኋላ በአጠቃላይ የፎርቹን ኤዲተሮች እኔን ጠፍጥፈው ሠርተውኛል ብል ማጋነን አይሆንም በሚል ያለፈበትን የጋዜጠኝነት ህይወት በአጭሩ ገልፆታል፡፡
#ከፎርቹን የሁለት ዓመታት ቆይታ በኋላ ሪፖርተር ጋዜጣን በመቀላቀል ለ18 ዓመታት ከከፍተኛ ሪፖርተርነት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለው ቃለየሱስ ከሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ጋር መሥራት መታደል ነው ይላል፡፡ከአቶ አማረ ጋዜጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአገር ፍቅርና ብሔራዊ ጥቅምን (National Interest)፣ደግነትንና ለሠራተኞቹ ያለውን ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ለጋዜጠኞች የሙያ ነፃነት ሰጥቶ ሠርቶ የሚያሠራበትን መልካም ትምህርት ቀስሜያለሁ ብሏል፡፡በሪፖርተር ሳለሁም በርካታ የሙያ ማሻሻያዎችንና የአጭር ጊዜ ሥልጠናዎችን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገሮች አግኝቻለሁ በማለት ትናንቱን ያመሰግናል፡፡
#በዘ -ሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ የማቀርባቸው ዘገባዎቼ በአብዛኛው ቢዝነስ ተኮር ነበሩ የሚለው ቃለየሱስ በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድን ዘርፎች ላይ አተኩር ስለነበር፤በእነዚህ ዙሪያ በሚሠሩ የውጭ መጽሔቶች ለእኛም ጻፍልን የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ ኤርላይን ፍሊት ማኔጅመንት፣ወርልድ ኤር ኒውስ፣ኤርላይን ኢኮኖሚክስ፣አፍሪካን ኤሮስፔስና ዓረቢያን ኤሮስፔስ፣አቪዬሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ፣አፍሪካን ቢዝነስ እና አፍሪካን ማይኒንግ ጆርናል ለተባሉ መጽሔቶች በፍሪላንስነት ለረዥም ዓመታት ሠርቻለሁ ይላል፡፡
እ.ኤ.አ.በ2008 በእንግሊዝ አገር በሚካሄድ “Best Aerospace Journalist of the Year” ሽልማት ታጭቼና ለንደን ተጋብዤ ዋናውን ሽልማት ባላሸንፍም፣"How Safe Are African Airlines?" በሚል ርዕስ በኤርላይን ፍሊት መጽሔት ላይ ያሳተምኩት ጽሑፍ ከ500 ለውድድር ከቀረቡ ጽሑፎች አምስቱ ምርጥ ውስጥ ለመግባት በመቻሉ፣ሰርተፊኬት ተበርክቶልኛል ብሏል፡፡
#በ2007 ዓ.ም. በትግራይ ሽመልባ የኤርትራ ስደተኞች መጠለያ ካምፕ ጉብኝት በማድረግ፣ ስለኤርትራዊያን ስደተኞች አሳዛኝ ሕይወት "The Woes of Eritrean Refugees” በሚል ርዕስ በዘ- ሪፖርተር ጋዜጣ ያሳተምኩት ሰፊ ጽሑፍ ጄኔቭ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) ዋና መሥሪያ ቤት ተመርጦ፣ለረዥም ጊዜ በድረ ገጻቸው ላይ ለንባብ ተቀምጦ ነበር፡፡በሻሸመኔ መልካ ኦዳ ስለሚገኙ የራስ ተፈሪያን ማኅበረሰቦች በቦታው ተገኝቼ የሠራሁት "The Plight of Rastafarians in Ethiopia" ዘገባ ከራስ ተፈሪያን ማኅረሰብ ምሥጋናና ዕውቅና አስገኝቶልኛል ይላል፡፡
ቃለየሱስን አንባቢያን የሚያውቁት ስለኢትዮጵያ አየር መንገድና በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ስለሚካሄዱ የማዕድንና የነዳጅ ፍለጋዎች ተከታታይ በርካታ ዜናዎችን በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በመሥራቱ ነው፡፡ ከዚያ ባለፈም ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ጋር የመሥራት ዕድሉን አግኝቷል፡፡
#የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ለሥራ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅትም እነሱን በማገዝ የተለያዩ ሥራዎችን ከውኗል፡፡ከእነዚህም መካከል “CNN, Aljazeera, SKY News, The Economics, National Geographic, Los Angeles Times, News Week, New York Times, Christian Science Monitor, Chicago Tribune…” እና ሌሎችም ከተሳተፈባቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡
እ.ኤ.አ. በ2019 አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን በተመለከተ ሲኤንኤን (CNN) በሠራቸው ዘገባዎች ላይ በረዳት ፕሮዲዩሰርነት የሠራ ሲሆን፣በወቅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከሲኤንኤን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ምሥጋና ተችሮታል፡፡በዘገባዎቹ ላይም ሙሉ ስሙን በማስፈር ተገቢውን ዕውቅና ሰጥተውታል፡፡የአሜሪካው አልጄዚራ ኢንግሊሽ ቡድን ስለአውሮፕላን አደጋው ዶክመንተሪ ለማዘጋጀት አደጋው ከደረሰ ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅትም፣አብሮ የአገር ውስጥ ፕሮዲዩሰር (Local Producer) ሆኖ ሠርቷል፡፡
መቼ ይሄ ብቻ ቃለየሱስ የ”Fault Lines” ፕሮግራም አዘጋጅ ከሆነው ጆሽ ረሺንግ (Josh Rushing) እና ፕሮዲዩሰሯ ካቢታ ቺኩሩ ጋር የሠሩት ዶክመንተሪ የተለያዩ አህጉሮችን የሸፈነ ሲሆን፣ለኤሚ አዋርድ ዕጩ ሆኖ ቀርቦም ነበር፡፡
#ከ18 ዓመታት አገልግሎት በኃላ እ.ኤ.አ. በ2020 ሪፖርተር ጋዜጣን ተሰናብቶ ኦሪጅንስ ሚዲያን በማቌቋምና ከኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት በመውሰድ፣‹‹ኢትዮ የንግድና የኢንቨስትመንት መድረክ››የተሰኘ ፕሮግራም በሳምንት ለሁለት ቀናት እያዘጋጀ ለሦስት ዓመታት ያህል አቅርቧል፡፡ኦሪጅንስ የሚል የጉዞ (Travel Magazine) ለማሳተም እየንቀሳቀሰ የነበረ ቢሆንም፣በኮቪድ ወረርሽኝና በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለፍሬ ሊበቃለት እንዳልቻለ በቁጭት ያስታውሳል፡፡
#ገጠመኞቹ
#ቃለየሱስ በጋዜጠኝነት ሙያ የገጠሙኝ ፈተናዎች ብዙ ናቸው ይላል፡፡ሙያው ራሱ የሚያስደስት ነገር እንዳለው ሁሉ ብዙ የሚያስጨንቁና የሚከብዱ ነገሮችም አሉት።ጋዜጠኛው ከህሊናው ጋር ተሟግቶና ሚዛኑን ጠብቆ የሚሰራው ነገር አንዱ ሲሆን።ዘገባን ወቅት ጠብቆ መስራትም የራሱ ፈተና አለው። ሚዛናዊነቱ ሳይጓደልም እንኳን ስለአንድ ነገር ሲፃፍ ወይም ሲዘገብ በዜናው ምከንያት የሚጠቀሙ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ።
ወዲህ ደግሞ ጉዳቱም የዛን ያህል ነው።አንድ ሚዲያ በሚሰራው ዘገባ ባለስልጣንም ሆነ ካምፖኒ ሊሆን ይችላል የነበረውን አቅም ሊያጣ ይችላል።ይህ የሚዲያ ባህሪ ነው።ፈተናዎቹ የበዙ ቢሆኑም ጋዜጠኛው ሲፅፍ ሚዛናዊነት የተለበሰ መሆን አለበት ባይ ነው ቃለየሱስ።
#ቃለየሱስ ረጅም ዓመት የሠራው ህትመት ሚዲያ ላይ ነው።በአንድ ወቅት ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛ ጋር ወደ ትግራይ በማቅናት በኢትዮ ኤርትራ ስላለው ሁኔታ ለመዘገብ አመሩ፡፡ሽሬ አካባቢ ሽመልባ የሚባል የኤርትራ ስደተኞች ያሉበትን ስፍራ ጎብኝተውና አነጋግረዋቸው ወደ ሽራሮ ሄዱ፡፡የጦርነቱ ከተማ ወደነበረችው ባድመ ሄደውም ነዋሪዎችን፣አርሶ አደሮችና የከተማውን አስተዳደር ቃኝተውና ቃለመጠይቅ አድርገው ወደ ኤርትራ ድንበር ተጠጉ፡፡
#የኤርትራን መሬት ከወንዝ ባሻገር እያዩና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ሲያስጎበኟቸው የተቀበሩ ፈንጂዎች ስለነበሩ በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሀይል አማካኝነት የፈንጂ ማስወገድ ስራው እየተሰራ ስለነበር የምንረግጠውን መንገድ ጠቆሙን ካለ በኋላ ቀይ ቀይ የተደረገባቸውን ድንጋዮች አሳይተውን ለእግር ፉካ የምትሆን ድንጋይ አሳዩን።ቀይ ምልክት የተደረገባቸውን ድንጋዮች ትተን ሌላ ከረገጥን ልንሞት እንደምንችል ነገሩን።በፈንጂ መሀከል በጭንቅና በዝግታ ያሳለፍንውን ምንጊዜም አልረሳውም ይላል ቃለየሱስ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ በአቬየሽን፣በነዳጅ እና ማዕድን ፍለጋ ስራዎች ዙሪያ ለመዘገብ ወደ ሱማሌ ክልል ይሄዳል፡፡ከኦጋዴን ነፃ አውጪ ጋር የነበሩ ውጊያዎች ስለነበሩ አንድ ጊዜ አቦሌ ከሚባል በደቡብ ምዕራብ በሚገኝ ኩባንያ የነዳጅ ስራ ፍለጋ በሚያደረግ ካምፕ ላይ ታጣቂዎቹ ጥቃት ሰንዝረው 9 ቻይናውያን እና ወደ 65 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ህይወት ያልፋል።
ያንን ለመዘገብ ወደ አካባቢው የሄደው ቃለየሱስ ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛው ፖልስ አሎቤ ጋር ያለ እንቅልፍ ረጅም ቀናት በማሳለፋቸው በሀሩራማው ኦጋዴን ውስጥ ለረጅም ሰአታት ራሱን ስቶ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና የነቃበትን ጊዜም ያስታውሳል።ቃለየሱስ ገጠመኞቹ የትየለሌ ናቸው፡፡በችሎት ዘገባ እንዲሁም ጋምቤላ ለዘገባ ሄዶ ያጋጠሙትንም ሁሌ እያስታወሰ ይገረምባቸዋል፡፡ በተለያዩ የአቪዬሽን ስብሰባዎችና እንዲሁም በአውሮፕላን አምራች ካምፓኒዎች በአካል እየተገኘም የሚያማልሉ ዘገባዎችን አስነብቧል፡፡
#ስለ ቃለየሱስ የታላላቅ ሰዎች ምስክርነቶች
"ቃለ ኢየሱስ በቀለ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በትጋት ከሠሩ ባለሙያዎች አንዱ ነው።" ይላል የሪፖርተር ጋዜጣ መስራች አማረ አረጋዊ። ምስክርነቱንም በመቀጠል፦
"... ቃለ ኢየሱስ በአቬሽን እና በማዕድን ዘገባዎች ላይ ያተኩር እንጁ የተሰጠውን ደስ ብሎት የሚሠራ ጋዜጠኛ ነው። የጋዜጠኝነት የሥነ ምግባር ደንብን አውቆ የሚተገብር ባለሙያ ነው። ፕሮፌሽናሊዝም እንዲሰፍን የሚታገል ጠንቃቃ ባለሙያ መሆኑን መመስከር እወዳለሁ።" በማለት ገልጿል
፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#የአቶ ግርማ ዋቄ ምስክርነት
#ቃለ ኢየሱስ በቀለን ረጅም ጊዜ አውቀዋለሁ። ለአቬሽን የተለየ ፍቅር አለው። አለምአቀፍ ኮንፈረንሶች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋል። ከዚያም በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ፅሁፍ ያቀርባል።ብስለቱ ይደንቃል። ከሌሎች የስሚ ስሚ ሰምቶ ሳይሆን አንድን ጉዳይ ከስር ከመሠረቱ አውቆ የመዘገብ ችሎታውን አደንቅለታለሁ። ስለ አፍሪካ አየር መንገድ ፣ ስለ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በወጉ ተረድቶ ስለሚፅፍም ፅሑፉ ተነባቢ ለመሆን ችሏል። ኢትዮጵያ ውስጥ አቬሽን ጋዜጠኝነት በጥልቀት ሲሠሪ የማውቀው እርሱን ነው።ሌሎችም አሉ። እርሱ ግን ከፍ አድርጎ በልህቀት የሚሠራ በመሆኑ ይለያል።
ገና አየር መንገድ ሲመጣ መረጃ ለማግኘት ፍላጎት ያሳያል። ዕውነትን ለማግኘት ይጎለጉላል። አፍሪካም ውስጥ ፈጠን ብሎ አቬሽን ጋዜጠኝነት ላይ የገባ በመሆኑ ይህም ግንባር ቀደም ያደርገዋል። ቃለኢየሱስ ካለበት ካናዳ ሆኖ የአቬሽን ጋዜጠኝነትን ሙያ እንዲያሳድግ ምክሬን እለግሰዋለሁ።
አቶ ግርማ ዋቄ
የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
‹‹እኔ ቃለየሱስ በቀለን የማውቀው ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ፎርቹን ጋዜጣ አብረን ስንሠራ ጀምሮ ነው›› የሚለው የሪፖርተር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው መላኩ ደምሴ ነው፡፡‹‹ከዚያም በኌላ ለ18 ዓመታት አብረን በሪፖርተር ጋዜጣ ሠርተናል፡፡ከጀማሪ ሪፖርተርነት አንስቶ እስከ አርታኢነት በዘለቀው የሥራ ጉዞው በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድናት ዘርፍ እጅግ በጣም በርካታ ዘገባዎችን የሠራ ሲሆን፣በሁሉም ሥራዎቹ አንጀት አርስ የሚባል ጋዜጠኛ ነው፡፡ጋዜጠኝነትን ከልቡ ከማፍቀሩ የተነሳ አብረው ለሚሠሩ ጋዜጠኞች ጭምር የሙያውን ፍቅር የማጋባት ችሎታ ያለው ነው፡፡ቃለየሱስ ዘገባዎችን ሲሠራ የሁሉንም ባለጉዳዮች ደምፅ ከማካተት በተጨማሪ፣አንባቢያን ለርዕሰ ጉዳዩ ቅርበት እንዲፈጥሩ የሚያስችል ስሜትን የተካነ ነው፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በአቪዬሽን ዘገባ በግንባር ቀደምነትነት የሚጠቀስ ጋዜጠኛ ማነው ቢባል በመጀመሪያው ረድፍ ላይ የሚገኘው ቃለየሱስ ነው፡፡በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያዎችን፣አየር መንገዶችን፣በአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሳይቀር በተለያዩ አገሮች በማግኘት በሪፖርቶቹ ውስጥ ድምፃቸውን ከማካተቱም በላይ በቃለ ምልልስ ጭምር ለአንባቢያን ተደራሽ በማድረግም ወደር የለውም፡፡የአውሮፕላን አደጋዎች ሲያጋጥሙም ሆነ የተለዩ ክስተቶች ሲኖሩ ከሚሠራቸው ዘገባዎች በተጨማሪ፣በተለያዩ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማብራሪያ የሚፈለገው ቃለየሱስ ነው፡፡በውጭ ለሚዘጋጁና ቁጥራቸው ቀላል ለማይባል የአቪዬሽን መጽሔቶች በርካታ ዘገባዎችን በመሥራትም ታዋቂ ነው፡፡
‹‹በማዕድናት ዘርፍም ከካሉብ ነዳጅ የጀመረው የጋዜጠኝነት ህይወቱ በተለያዩ ክልሎች የሚደረጉ የነዳጅ፣የወርቅ፣የብረት፣የፖታሽ፣የታንታለም፣የኦፓልና ሌሎች የከበሩ ማዕድናት ፍለጋ ሥራዎችን በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታዎች፣በጂኦ ተርማል ፕሮጀክቶች፣ በፀሐይና በንፋስ ኃይል ማመንጫዎች፣በሲሚንቶና በሌሎች የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም ሰፋፊ ዘገባዎችን በማበርከት ስመጥር ሆኖ ዘልቌል፡፡በፖለቲካው መስክ ደግሞ በተለያዩ አገራዊ ምርጫዎች ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎች ተሰማርቶ አመርቂ ሪፖርቶችን በማቅረብ ችሎታውን ማስመስከር የቻለ ነው፡፡ከሪፖርተር በገዛ ፈቃዱ ከተሰናበተ በኃላም በኤፍኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት ወስዶ ያቀርባቸው የነበሩ የቢዝነስ ፕሮግራሞቹ፣የቃለየሱስን ችሎታ ከጋዜጣ አንባቢያን ወደ ሬዲዮ አድማጮች በማዝለቅ ረገድ ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ነበሩ፡፡
‹‹ቃለየሱስ ግልጽ፣ ቅን፣ ሰብዓዊነትን የሚያስቀድም፣ኃላፊነት የሚሰማው፣ በአስገራሚ ትውስታው የረሳናቸውን ጉዳዮች የማስታወስ ችሎታ ያለው፣በቀልድም ሆነ በቁምነገር የሚታወቅ፣ ከማንኛውም ሰው ጋር ወዳጅነት ለመፍጠር ምንጊዜም ዝግጁ የሆነ፣በተለይ በሪፖርተር የሥራ ባልደረቦቹ ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ምሥጉን ጋዜጠኛ ነው፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው ሰፊና ጥልቅ ትንተናዎቹ የሚታወቅ ሲሆን፣ብዙዎችም በዚህ መጠን ለነገሮች ትኩረት ሰጥቶ የማስረዳት ብቃቱን በአድናቆት የሚመሰክሩለት ነው፡፡እኔም ከሁለት አሠርት ዓመታት በላይ አብሬው ስለሠራሁ ችሎታውን በዚህ መጠን ስገልጽ በከፍተኛ ስሜት ሲሆን፣ይህንን ከመሰለ ብርቱና ታታሪ ጋዜጠኛ ጋር የመሥራት ዕድል በማግኘቴ በእጅጉ ደስተኛ ነኝ›› በማለት መላኩ ምስክርነቱን አጠቃሏል፡፡
ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው ስለ ቃለየሱስ በሰጡት ምሥክርነት ‹‹እኔ እሱን ለአየር መንገዱ ልዩ እንደ ሆነ ሰው አየዋለሁ።በጣም ትሁት፣አዳማጭ የሆነ ሰው ነው።ከየት እንዳመጣው ባላውቅም ልዩ የሆነ የኢንግሊዘኛ ፀሀፊ ነበር።በሁለት ምክንያት የሱን ፅሁፍ አነብ ነበር፡፡አንዱ በፅሁፉ ለመደሰትና እንደ ግጥም ስለምወደው ነው።ሌላው ከእውቀቱ ወይም አንብቦም ይሁን ባላውቅም የፅሁፎቹ ይዘት በሚያውቀው ነገር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው።በዚህም በጣም አበረታታዋለሁ።
‹‹ከተዋወቅን 15 ዓመታት ሆኖናል።በውጪ ህትመቶች ላይ የሚያወጣቸው ስራዎች ቃለየሱስ ብሎ ስሙ ይገለፅ ይሆናል እንጂ ማንም ነጭ የሚፅፈው አይነት ፅሁፍ ነው።የፅሁፉ ይዘትና አያያዝ ደረጃውን የጠበቀ ነው።የሚፅፍባቸው መፅሄቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ትላልቅ ናቸው።ነገር ግን ደረጃቸውን ጠብቀዋል የሚባሉትም አንዳንዴ ትርኪምርኪ ሲፅፉም ይታያል።ግን የሱ ፅሁፍ በጣም የሚያኮራ ነው።ሌላው ዜግነቱን የሚወድ ሰው ነው።ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለኢትዮጵያ አየርመንገድ በቦታው ካሉት ህዝብ ግንኙነቶች እሱ ብዙ የሰራ ይመስለኛል።እውቅናና ሽልማት ሊሰጠው በርታ ሊባል የሚገባው ልጅ ነው።ወገቡን ይዞ ነበር ለአየር መንገዱ ይሰራ የነበረው።አሁንም ቢሆን ባለበት ሆኖ ለአየርመንገዱ ነገሮችን መስመር የሚያሲዝ ሰው ነው››ብለዋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨
የቀድሞ የሲቪል አቬሽን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወሰንየለህ ሁነኛው በበኩላቸው ‹‹ከተዋወቅን ከ7 ዓመት በላይ ይሆነናል።እኔ ከማቃቸው የሚዲያ ሰዎች በጋዜጠኝነት የሱን ያህል ብዙም አቬሽን ዘርፉ ላይ ገብቶ እያንዳንዱን ነገር አይቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይሁን የግል ኦፕሬተሮቹም ጋር እንደሱ የሚፅፍ አላየሁም።እሱ ነው የተሻለ ጠይቆ አንብቦ ተረድቶ አስተዋጽዖ ለማድረግ የሚጥረው።በዛ ወቅት ቃለ እየሱስ ጥሩ ዘጋቢ ነበር።ብዙ መፅሄቶች ላይ ይሳተፋል አንዳንድ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ላይ ይሄዳል። በኢትዮጵያ አየርመንገድና በሲቪል አቬየሽን ላይ የተለየ እውቀት ያለው ነው።ምክንያቱም በየእለቱ ስለሚከታተል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አቬየሽን ኢንዱስትሪ በደንብ ያውቀው ነበርና ነው።
‹‹አቬየሽን ኢንዱስትሪው በእነዚህ መፅሄቶች በብዙ መንገድ ይጠቀማል።ህብረተሰቡ አቬየሽኑም ሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራሱን ከማስተዋወቁ በላይ ምን ላይ እንዳለ እና በተለየ አካል እንዲሰራለት ትክክለኛነቱን ይረጋገጣል።እንዲሁም ምን ያህል የግል ኦፕሬተሮች ምን ያህል በኢኮኖሚው ይሳተፋሉ የሚለውንም ለህብረተሰቡም ለመንግስትም መረጃ ይሰጣል።ስራዎቹ ለብዙ ነገሮች የመረጃ ምንጮች ሆነው ያገለግላሉ ።
‹‹ቃለእየሱስ በዚያ ወቅት የሚያደርገው የኢትዮጵያን አቬየሽን ኢንዱስትሪ ከሌላው እያነፃፀረ በሚያውቀው ልክ ለህብረተሰቡ ሙሉ መረጃ ይሰጣል።ለግል ኦፕሬተሮችም ለኢትዮጵያ አየር መንገድም ግብዐት የሚሆኑ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል።በተዘዋዋሪም ያስተዋውቃል።እውነተኛ መረጃ ሲያቀርብ ሰው ስለ አቬየሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እውቀት ያዳብራል።አብዛኛው ሰው ስለ ግል ኦፕሬተር አያውቅም አውሮፕላን አላቸው ወይ ? ብሎ የሚጠይቅም ብዙ ሰው ነው።በዚህ ጉዳይ ላይ በብዛት የሚሰራው ቃለእየሱስ ነበር››ብለዋል፡፡
‹‹በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ የቃለየሱስ አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።››ብለው ምስክርነታቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፡፡‹‹ቃለየሱስና እኔ ለረጅም ጊዜ እንተዋወቃለን በ«Reporter» ጋዜጣ ሲሰራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜናዎችንና እድገቶችን ይዘግብ ነበር።በቀጣይ የአቪዬሽን ዘርፍ ላይ ጥልቅ ፍላጎት አሳየ፤እኛም ከIATA ጋር እንዲገናኝ አደረግነው፣በተለይም በየዓመቱ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚካሄዱ የIATA አመታዊ አጠቃላይ ጉባኤዎች (AGM) ላይ የፕሬስ ኮንፈረንሶች ላይ ይሳተፍ ነበር።
‹‹በአፍሪካ አየር እና አቪየሽን (African Aerospace and Aviation) መጽሔት እና በሌሎች ከአቪየሽን ጋር የተያያዙ መጽሔቶች ላይ ጽሁፎችን ይጽፍ ነበር።በአጋርነትም ብዙ ፕሮጀክቶችን አከናውነናል። እኔም የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድ ሊቀመንበር በነበርኩበት ሰዓት፣የራሱን የጉዞና ቱሪዝም መጽሔት እንዲጀምር ወይም እንዲያስብበት ሀሣብ አቀርብለት ነበር፤እርሱም ይህን ሀሳብ በአዎንታ ይመልከተው ነበር።
‹‹በአጠቃላይ፣ ይህ ዘርፍ እስከዛሬም በቂ የሚዲያ ሽፋንና የማስተዋወቂያ መድረክ ስላልነበረው፣ ቃለየሱስ ይህን ክፍተት ልብ ብሎ በማጤን በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል።በእኔ አመለካከት፣ያበረከተው አስተዋፅኦ አስደናቂ ነው፣ለሥራውም እውቅናና ምስጋና ሊቀርብለት ይገባል››ብለዋል፡፡
ሲጠቃለል ከ15 አመት በላይ በአለም አቀፍ የአቪየሽን ስብሰባዎችን በአሜሪካ፣አውሮፓ፣አፍሪካ፣ መካከሉኛው ምስራቅ እና ኤሽያ ተሳትፌያለሁ 36 ሃገሮችንም የማየት እድል ገጥሞኛል የሚለው የአቪየሺን ባለወርቃማ ብዕሩ ቃለየሱስ በቀለ እ.ኤ.አ.ከ2023 መጨረሻ ጀምሮ ኑሮውን በካናዳ ያደረገ ሲሆን፤ለአፍሪካ ኤሮስፔስና አቪየሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ በፍሪላንስነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
8 months ago
#ethiopia ሞሮኮ የአፍሪካን የእግርኳስ አባት አመሰገነች !
ሀገሩ የናቀቻቸዉ ሞሮኮ ያከበረችዉ ታላቅ ሰዉ !
#ethiopia | እነሆ ወትሮም ቱሪስት የሚወዳት ሞሮኮ " Africa is calling " በሚል መፈክር የጠራቻቸዉ እንግዶቿ ወደሀገሪቱ ጎርፈዋል ። ካዛብላንካ እና ራባትን ጨምሮ በዘጠኝ ውብ ከተሞቿ ደምቀዋል ።
የጥቋቁር ክዋክብቶቹ የእግር ኳስ ዳንኪራ በሆነው ይህ ለ35ኛ ጊዜ የሚዘጋጀዉ የአህጉሩን መድረክ ሀሳብ አፍልቃ እዉን ያደረገችዉ መስራቿ ኢትዮጵያ በሌለችበት 24 ሀገራት በ6 ምድብ ለአንድ ዋንጫ ይፋለማሉ ። ከዚህ ሚሊዮኖች በጉጉት የሚከታተሉት ሁነት ጀርባ አንድ ሁገርና አንድ ታላቅ ሰዉ አሉ ።
ነገርን ከስሩ እንዲሉ አበዉ ጥቂት ወደኋላ እንመለስ ።የአፍሪካ ዋንጫ በደረሰ ቁጥር አፍሪካውያን ከእነሱ ጋር እኩል እንዳልሆኑና በነጮች ጨለማው በተባለው አህጉር፣ ህዝቦቿ የባርነት ቀንበር በሚማምቅቁባት ዘመን አፍሪካ አንድ የራሷ የስፖርት መድረክ ያስፈልጋታል በሚል በ1957 ካርቱም ምስረታውን አደረገ ።
እነሆ ይህ መድረክ ከሀምሳ አመታትን በላይ ተሻግሮ ነዉ በትላንትናው እለት ለ 35ኛ ጊዜ በሞሮኮ የተጀመረው ።
የያኔዉ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ በመጀመሪያዎቹ ጊዚያት ቀላል አልነበሩም ።
በዚህ ወድድር ደቡብ አፍሪካ በአፓርታይድ ፖሊሲ ምክንያት ብሄራዊ ቡድኗ ነጭ ተጫዋቾችን ብቻ በመምረጧ ከወድድሩ እንደትወጣ መደረጓ ምን ያህል ጥቁሮች አይገባንም የሚል አስተሳሰብ እንደነበራቸዉ ገላጭ ነዉ ።
ለማንኛውም በጊዜዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከተፅዕኖ ፈጣሪ ፊታውራሪዎቹ ውስጥ ይገኝ ነበር ።
እንዲሁም በግለሰቤ ደረጃ ለአፍሪካ እግር ኳስ መወለድና ማበብ የኢትዮጵያ አበርክቶ በአንድ ግለሰብ አመራር ሰጪነት አማካኝነት ከፍ ያለ ቦታም ይዞ እናገኘዋለን ፤ በዚህም የተነሳ እኝህ ኢትዮጵያዊ ‘የአፍሪካ የእግር ኳስ አባት’ የሚል ስያሜ እስከማግኘት የደረሱ አንድ ታላቅ ሰዉ አሉ ።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለምሰረታ በቅቶ ዛሬ ላይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ሁሉም ሃገራትን እንዲሳተፉ ማድረግ እንዲችል አንድ ታላቅ ኢትዮጲያዊ ሚናቸው ቀላል አልነበርም ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ።
እርግጥ ነዉ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለምሰረታ በቅቶ ዛሬ ላይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ሁሉም ሃገራትን እንዲሳተፉ ማድረግ እንዲችል አንድ ታላቅ ኢትዮጲያዊ ልፋትና ጥንካሬ አለ እሳቸዉም ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸዉ ብለህ አለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀውን ታሪክ ለአንድ ኢትዮጵያዊ የኳስ አፍቃሪ ማንነታቸውን ብትጠይቅ በቅጡ አይነግርህም።
ለማንኛውም እኒህ ታላቅ የስፖርት ሰው የእግር ኳስ ተጨዋች፤ አሰልጣኝ፤ አስተማሪ፤ የቡድን መሪ፤ ኮሜንታተር፤ የስነ ልቦና ባለሙያ እና በተለያዩ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የስፖርት መድረኮች ፕሬዝዳንት ሆነው ያገለገሉት ታላቅ ሰዉ ናቸዉ ።
ክቡር ይድነቃቸው ተሰማ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን CAF ምስረታ ላይ የአንበሳውን ድርሻ የተወጡ ታላቅ ሰዉ ።
ተቋሙንም ለ14 ዓመታት በፕሬዝደንት በብቃት የመሩ ዛሬም ድረስ CAF የሚመራባቸው አብዛኞቹ ሕጎችም በክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ክቡር አቶ ይድነቃቸው አፍሪካ በዓለም ዋንጫ የመካፈል መብት እንደታገኝ ከፊፋ ጋር ለብዙ ዓመታት ታግለዋል። የትንባሆና የአልኮል ማስታወቂያዎች በአፍሪካ ስታድየሞች እንዳይሰቀሉ ፣ እንደ ድርጅት አፓርታይድን በሰፋት ተቃውመዋል ፣ የአፍሪካ ዳኞች እና ኮሚሽነሮች የአለም አቀፍ ውድድሮች ልምድ እንዲቀስሙ አድረገዋል። ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ለአፍሪካ እግር ኳስ ከሰሯቸው ከብዙ በጥቂቱ ናቸው።
ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፊደሬሽን እና ለአፍሪካ እግር ኳስ ላበርከተቱ አስተዋጾ በሃገራቸው አንድ መታሰቢያ ባይቆምላቸውም በሞሮኮ ንጉሥ ሐሰን ዳግማዊ በተሰጠ መመርያ ግን በ1981 አም በካዛብላንካ የሚገኝ ስታዲየም በስማቸው እንዲሰየምላቸው ተደርጓል ። ሀገሬ ያላት ሀገሩ ግን ምንም አላደረገችለትም ።
#ታዴ_የማመይ_ልጅ
ሀገሩ የናቀቻቸዉ ሞሮኮ ያከበረችዉ ታላቅ ሰዉ !
#ethiopia | እነሆ ወትሮም ቱሪስት የሚወዳት ሞሮኮ " Africa is calling " በሚል መፈክር የጠራቻቸዉ እንግዶቿ ወደሀገሪቱ ጎርፈዋል ። ካዛብላንካ እና ራባትን ጨምሮ በዘጠኝ ውብ ከተሞቿ ደምቀዋል ።
የጥቋቁር ክዋክብቶቹ የእግር ኳስ ዳንኪራ በሆነው ይህ ለ35ኛ ጊዜ የሚዘጋጀዉ የአህጉሩን መድረክ ሀሳብ አፍልቃ እዉን ያደረገችዉ መስራቿ ኢትዮጵያ በሌለችበት 24 ሀገራት በ6 ምድብ ለአንድ ዋንጫ ይፋለማሉ ። ከዚህ ሚሊዮኖች በጉጉት የሚከታተሉት ሁነት ጀርባ አንድ ሁገርና አንድ ታላቅ ሰዉ አሉ ።
ነገርን ከስሩ እንዲሉ አበዉ ጥቂት ወደኋላ እንመለስ ።የአፍሪካ ዋንጫ በደረሰ ቁጥር አፍሪካውያን ከእነሱ ጋር እኩል እንዳልሆኑና በነጮች ጨለማው በተባለው አህጉር፣ ህዝቦቿ የባርነት ቀንበር በሚማምቅቁባት ዘመን አፍሪካ አንድ የራሷ የስፖርት መድረክ ያስፈልጋታል በሚል በ1957 ካርቱም ምስረታውን አደረገ ።
እነሆ ይህ መድረክ ከሀምሳ አመታትን በላይ ተሻግሮ ነዉ በትላንትናው እለት ለ 35ኛ ጊዜ በሞሮኮ የተጀመረው ።
የያኔዉ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ በመጀመሪያዎቹ ጊዚያት ቀላል አልነበሩም ።
በዚህ ወድድር ደቡብ አፍሪካ በአፓርታይድ ፖሊሲ ምክንያት ብሄራዊ ቡድኗ ነጭ ተጫዋቾችን ብቻ በመምረጧ ከወድድሩ እንደትወጣ መደረጓ ምን ያህል ጥቁሮች አይገባንም የሚል አስተሳሰብ እንደነበራቸዉ ገላጭ ነዉ ።
ለማንኛውም በጊዜዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከተፅዕኖ ፈጣሪ ፊታውራሪዎቹ ውስጥ ይገኝ ነበር ።
እንዲሁም በግለሰቤ ደረጃ ለአፍሪካ እግር ኳስ መወለድና ማበብ የኢትዮጵያ አበርክቶ በአንድ ግለሰብ አመራር ሰጪነት አማካኝነት ከፍ ያለ ቦታም ይዞ እናገኘዋለን ፤ በዚህም የተነሳ እኝህ ኢትዮጵያዊ ‘የአፍሪካ የእግር ኳስ አባት’ የሚል ስያሜ እስከማግኘት የደረሱ አንድ ታላቅ ሰዉ አሉ ።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለምሰረታ በቅቶ ዛሬ ላይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ሁሉም ሃገራትን እንዲሳተፉ ማድረግ እንዲችል አንድ ታላቅ ኢትዮጲያዊ ሚናቸው ቀላል አልነበርም ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ።
እርግጥ ነዉ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ለምሰረታ በቅቶ ዛሬ ላይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ሁሉም ሃገራትን እንዲሳተፉ ማድረግ እንዲችል አንድ ታላቅ ኢትዮጲያዊ ልፋትና ጥንካሬ አለ እሳቸዉም ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸዉ ብለህ አለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀውን ታሪክ ለአንድ ኢትዮጵያዊ የኳስ አፍቃሪ ማንነታቸውን ብትጠይቅ በቅጡ አይነግርህም።
ለማንኛውም እኒህ ታላቅ የስፖርት ሰው የእግር ኳስ ተጨዋች፤ አሰልጣኝ፤ አስተማሪ፤ የቡድን መሪ፤ ኮሜንታተር፤ የስነ ልቦና ባለሙያ እና በተለያዩ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የስፖርት መድረኮች ፕሬዝዳንት ሆነው ያገለገሉት ታላቅ ሰዉ ናቸዉ ።
ክቡር ይድነቃቸው ተሰማ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን CAF ምስረታ ላይ የአንበሳውን ድርሻ የተወጡ ታላቅ ሰዉ ።
ተቋሙንም ለ14 ዓመታት በፕሬዝደንት በብቃት የመሩ ዛሬም ድረስ CAF የሚመራባቸው አብዛኞቹ ሕጎችም በክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ክቡር አቶ ይድነቃቸው አፍሪካ በዓለም ዋንጫ የመካፈል መብት እንደታገኝ ከፊፋ ጋር ለብዙ ዓመታት ታግለዋል። የትንባሆና የአልኮል ማስታወቂያዎች በአፍሪካ ስታድየሞች እንዳይሰቀሉ ፣ እንደ ድርጅት አፓርታይድን በሰፋት ተቃውመዋል ፣ የአፍሪካ ዳኞች እና ኮሚሽነሮች የአለም አቀፍ ውድድሮች ልምድ እንዲቀስሙ አድረገዋል። ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ለአፍሪካ እግር ኳስ ከሰሯቸው ከብዙ በጥቂቱ ናቸው።
ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፊደሬሽን እና ለአፍሪካ እግር ኳስ ላበርከተቱ አስተዋጾ በሃገራቸው አንድ መታሰቢያ ባይቆምላቸውም በሞሮኮ ንጉሥ ሐሰን ዳግማዊ በተሰጠ መመርያ ግን በ1981 አም በካዛብላንካ የሚገኝ ስታዲየም በስማቸው እንዲሰየምላቸው ተደርጓል ። ሀገሬ ያላት ሀገሩ ግን ምንም አላደረገችለትም ።
#ታዴ_የማመይ_ልጅ
8 months ago
ጋዛ ፈገግታዋ ታዬ ታላቁ የህብረት ጋብቻ ተፈፀመ !
ጠባቧ የጋዛ ሰርጥ ከፈገግታና ከሳቅ ከፍስሐና ደስታ ጋር የተለያየችዉ እንደ አዉሮጳዉያኑ አቆጣጠር ጥቅምት 2023 ነበር ።
የሐማስ ታጣቂዎች ጥቅምት 7፣ 2023 ደቡባዊ እስራኤልን አጥቅተዉ- 1200 ሰዎችን ገደሉ፤ ከ200 በላይ አገቱ ።
ይህን ተከትሎ እስራኤል የአጸፋ ርምጃውን ከጀመረች ጀምሮ ወደ ጋዛ ሰርጥ ምግብ ውኃና መድኃኒትን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች እንዳይገቡ በመከልከል በጀመረችው ዘመቻ የዚያች ትንሽ፣ ጠባብ፣ ደሐ ሰርጥ ቦምብ-ሚሳዬል እየተዘራባት ፣ፍርስራሽ እየተከመረባት ፣የቦምብ-ሚሳዬል ወዠብ ይወርድ ገባ ።
ዲፕሎማቶች በየመገናኛ ዘዴ-ጉባኤ-ስብሰባዉ የኃይማኖት መሪዎች በየፀሎት፣ ሶላታቸዉ ወቅት፣ከሳንቲያጎ ደ ቼሌ እስከ ኦታዋ፣ ከሲድኒ እስከ ሰነዓ የሚገኘዉ ሕዝብ በየአደባባይ ሰላም እንዲሰፍን የቀረቡ ሀሳቦች በሁለቱም ተፋላሚዎች ጀሮ ዳባ ልበስ ተብለዉ ከሁለት አመታት በላይ መአት ወረደባት ።
ጎስቋሎች ሕፃን-ካዋቂ፣ ወንድ ከሴት ሳይለይ ሽዎችን ህይወት የነጠቀው ጦርነት ሰርክ በባሩድ ጭስ ስለማይለያት አይደለምና ወግ ማዕረግ ለማየት ለመኖር ስጋት ሁና ከርማለች ።
እልፎች አልፈዉ ብዙዎች አልቀው የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ከጥይት ኳኳታ ከመድፍ ድምድምታ ተንፈስ ያለችው በደቡባዊ ጋዛ የምትገኘው የካን ዩኒስ ከተማ በአቡ ዳቢ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ድጋፍ የተደረገለት በጦርነት የፈራረሱ ህንጻዎች መሃል 54 ጥንዶች የተሞሸሩበት የጅምላ ሰርግ አድርጋለች ።
በእለተ ማክሰኞ ነጭ፣ ቀይ እና አረንጓዴ ባህላዊ ቀሚስ የተዋቡ ጥንዶችኝ የያዙ መኪኖች ሰልፍ በፈረሱ ሕንፃዎች ውስጥ እየተንሸራሸሩ አለምህ ዛሬ ነዉ ሲጨፈር ዉሏል ።
ወትሮም ለፍልስጤማውያን፣ ሰርጎች ብዙውን ጊዜ ለቀናት የሚቆዩ የተንቆጠቆጡ ክብረ በዓላት ናቸዉና የፍልስጤምን ባንዲራ በዙሪያቸው ያሉ ቤተሰቦች በሙዚቃ ሲጨፍሩ
ጥንዶቹ እና የሚወዷቸው ቤተሰቦቻቸዉ አስደሳች ጭፈራዎችን እና ሰልፎች ሀይሎጋን ሲጨፍሩ ታይተዋል ።
ይህ በሃማድ መኖሪያ አካባቢ በፈረሱ ሕንፃዎች ፍርስራሽ ውስጥ የተካሄደው ሥነ ሥርዓት የተካሄደው በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ "ጋላንት ናይት 3" የሰብአዊነት ዘመቻ ስር ነው ሲል የአናዶሉ ዘጋቢ ዘግቧል።
ሀጫ በረዶ የመሰለ ቬሎና ሱፍ የለበሱት ተጋቢዎች መካከል የሆኑት ላውዋ እና ኢማን፣ ሠርጉ ለዓመታት ከመከራ በኋላ ትንሽ እፎይታ እንደሰጣቸው ተናግረዋል።
ኤማን በጦርነቱ ወቅት የተገደሉትን አባቷን፣ እናቷን እና ሌሎች የቤተሰቧን አባላት በማጣታቸው ዉስጧ ሀዘን ቢኖም ሞትና ሰርግ የህይወት ኡደት በመሆናቸው ተመስገን ስትል ተደምጣለች ።
"እንዲህ ካለው ሀዘን በኋላ ደስታን ማግኘት ከባድ ነው" አለች እንባዋ እየፈሰሰ። "እግዚአብሔር ቢፈቅድ፣ ጡብ በጡብ እንገነባለን" ብላለች።
ቤተሰቦች እና የማህበረሰብ መሪዎች አዲስ ተጋቢዎችን በሰልፍ ሲመለከቱ የፍልስጤም ባንዲራዎች፣ አበቦች እና ባህላዊ ዘፈኖች ታጅበዉ ወልደው እንዲከብዱ ምኞታቸውን ገልፀዋል ሲሉ ያስነበቡት አናዶሉ አረብያ ኒዉስ ዘጋርዲያን ናቸዉ ።
ጠባቧ የጋዛ ሰርጥ ከፈገግታና ከሳቅ ከፍስሐና ደስታ ጋር የተለያየችዉ እንደ አዉሮጳዉያኑ አቆጣጠር ጥቅምት 2023 ነበር ።
የሐማስ ታጣቂዎች ጥቅምት 7፣ 2023 ደቡባዊ እስራኤልን አጥቅተዉ- 1200 ሰዎችን ገደሉ፤ ከ200 በላይ አገቱ ።
ይህን ተከትሎ እስራኤል የአጸፋ ርምጃውን ከጀመረች ጀምሮ ወደ ጋዛ ሰርጥ ምግብ ውኃና መድኃኒትን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች እንዳይገቡ በመከልከል በጀመረችው ዘመቻ የዚያች ትንሽ፣ ጠባብ፣ ደሐ ሰርጥ ቦምብ-ሚሳዬል እየተዘራባት ፣ፍርስራሽ እየተከመረባት ፣የቦምብ-ሚሳዬል ወዠብ ይወርድ ገባ ።
ዲፕሎማቶች በየመገናኛ ዘዴ-ጉባኤ-ስብሰባዉ የኃይማኖት መሪዎች በየፀሎት፣ ሶላታቸዉ ወቅት፣ከሳንቲያጎ ደ ቼሌ እስከ ኦታዋ፣ ከሲድኒ እስከ ሰነዓ የሚገኘዉ ሕዝብ በየአደባባይ ሰላም እንዲሰፍን የቀረቡ ሀሳቦች በሁለቱም ተፋላሚዎች ጀሮ ዳባ ልበስ ተብለዉ ከሁለት አመታት በላይ መአት ወረደባት ።
ጎስቋሎች ሕፃን-ካዋቂ፣ ወንድ ከሴት ሳይለይ ሽዎችን ህይወት የነጠቀው ጦርነት ሰርክ በባሩድ ጭስ ስለማይለያት አይደለምና ወግ ማዕረግ ለማየት ለመኖር ስጋት ሁና ከርማለች ።
እልፎች አልፈዉ ብዙዎች አልቀው የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ከጥይት ኳኳታ ከመድፍ ድምድምታ ተንፈስ ያለችው በደቡባዊ ጋዛ የምትገኘው የካን ዩኒስ ከተማ በአቡ ዳቢ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ድጋፍ የተደረገለት በጦርነት የፈራረሱ ህንጻዎች መሃል 54 ጥንዶች የተሞሸሩበት የጅምላ ሰርግ አድርጋለች ።
በእለተ ማክሰኞ ነጭ፣ ቀይ እና አረንጓዴ ባህላዊ ቀሚስ የተዋቡ ጥንዶችኝ የያዙ መኪኖች ሰልፍ በፈረሱ ሕንፃዎች ውስጥ እየተንሸራሸሩ አለምህ ዛሬ ነዉ ሲጨፈር ዉሏል ።
ወትሮም ለፍልስጤማውያን፣ ሰርጎች ብዙውን ጊዜ ለቀናት የሚቆዩ የተንቆጠቆጡ ክብረ በዓላት ናቸዉና የፍልስጤምን ባንዲራ በዙሪያቸው ያሉ ቤተሰቦች በሙዚቃ ሲጨፍሩ
ጥንዶቹ እና የሚወዷቸው ቤተሰቦቻቸዉ አስደሳች ጭፈራዎችን እና ሰልፎች ሀይሎጋን ሲጨፍሩ ታይተዋል ።
ይህ በሃማድ መኖሪያ አካባቢ በፈረሱ ሕንፃዎች ፍርስራሽ ውስጥ የተካሄደው ሥነ ሥርዓት የተካሄደው በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ "ጋላንት ናይት 3" የሰብአዊነት ዘመቻ ስር ነው ሲል የአናዶሉ ዘጋቢ ዘግቧል።
ሀጫ በረዶ የመሰለ ቬሎና ሱፍ የለበሱት ተጋቢዎች መካከል የሆኑት ላውዋ እና ኢማን፣ ሠርጉ ለዓመታት ከመከራ በኋላ ትንሽ እፎይታ እንደሰጣቸው ተናግረዋል።
ኤማን በጦርነቱ ወቅት የተገደሉትን አባቷን፣ እናቷን እና ሌሎች የቤተሰቧን አባላት በማጣታቸው ዉስጧ ሀዘን ቢኖም ሞትና ሰርግ የህይወት ኡደት በመሆናቸው ተመስገን ስትል ተደምጣለች ።
"እንዲህ ካለው ሀዘን በኋላ ደስታን ማግኘት ከባድ ነው" አለች እንባዋ እየፈሰሰ። "እግዚአብሔር ቢፈቅድ፣ ጡብ በጡብ እንገነባለን" ብላለች።
ቤተሰቦች እና የማህበረሰብ መሪዎች አዲስ ተጋቢዎችን በሰልፍ ሲመለከቱ የፍልስጤም ባንዲራዎች፣ አበቦች እና ባህላዊ ዘፈኖች ታጅበዉ ወልደው እንዲከብዱ ምኞታቸውን ገልፀዋል ሲሉ ያስነበቡት አናዶሉ አረብያ ኒዉስ ዘጋርዲያን ናቸዉ ።
8 months ago
መድፈኞቹ Vs
ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች
#ethiopia | ማይክ አርቴታ ከደርቢው ጨዋታ አንድ ነጥብ ለመጋራት ብሪጅ የደረሰ መሰለ ። ከ55 ደቂቃዎች በላይ የነበረውን የተጨዋች ብልጫ አድቫንቴጅ ተከትሎ የተፈጠረለትን ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ አጋጣሚ አመከነ ። የመድፉ አለቃ ማይክ አርቴታ ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠም ፈፀመ ። አርሰናል ከቼልሲ 10 ኮኮቦች ፊት የነበረው የተቀዛቀዘ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጨዋታ ሜንታሊቲና ፍላጎት ብዙዎችን እንዳነገጋረ ለንደን ደርቢን በአቻ ውጤት ፈፅሟል ።
ከዋና ኮኮቡ ካይሲዶ ቀይ ካርድ በኋላ ሚስተር ቼልሲ በጨዋታው ይቸገራል ሲባል ጭራሽ አንሰራራ ። ከቀይ ካርዱ በኋላ የማሬስካ የጨዋታ ቀመር ከመድፉ ፊት የተሳካ ሆነ ። ከዕረፍት መልስ ቼልሲ 1ለዐ በቻሎባ ጎል ቀድሞም መራ ። ከአምበሉ ኦዴጋርድ ቅያሪ ተፅእኖ ጋር አርሰናል 1ለ0 የተመራውን ጨዋታ ወደ አንድ አቻ ውጤት በሜሬኖ ጎል በብርሃን ፍጥነት ቀየረ ። መድፉ የአቻዋን ጎል ተከትሎ በዛው የጀመረውን የማጥቃት ቴምፖ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲባል ግን መልሶ በጨዋታው ከማሬስካ ተደናቂ ጨዋታን የማስተዳደር ታክቲካል ማስተር Class አቅም ጋር ደበዘዘ ። የቼልሲ ኮኮቦች ውጤቱን ይዞ ለመውጣት የነበራቸው የተሳካ የደርቢው ፍጥጫ Dark Art እንቅስቃሴ ውስጥ አርሰናል እንደተመሰጠ ቀረ ።
ከጨዋታው ጅማሮ አንስቶ በፀብ አጫሪ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ እንቅስቃሴ ዝግጁነት መድፈኛውን በደርቢው ቀን በብሪጅ ያስተናገደው ቼልሲ የገጠመውን የካይሲዶ ቀይ ካርድ ተከትሎ በ10 ተጨዋች ሳይቸገር የተሻለም ተንቀሳቅሶ መደፈኛውን አፈዘዘ ። ቼልሲ አርሰናል የሲዝኑ ውጤታማ አጀማመሩን ተከትሎ በአድናቆት ቃላት አጀብ ብቻ የቆየው የሊጉ መሪ መድፈኞች እስካሁን ያልታዩ ሰፊ የቡድን ክፍተቶችን አንፀባረቀ ። አርሰናል ያለ ዋና ዋና የተከላካይ መስመር ደጀኖቹ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ወትሮም እንደተጠበቀው ተቸገረ ። በዴክላን ራይስ ሕያው አስደናቂ ተጋድሎ ሰፊ ከላላ ተደርጎላቸውም ከቼልሲ የማጥቃት እንቅስቃሴ ፊት የሳሊባ እና ማጋሊሽ አልጋወራሾች ሲወከቡ አመሹ ። ግብ ጠባቂው ዴቪድ ሬያም ያለ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ያለ ስራ እንደተቀመጠ 90 ደቂቃውን የመጨረስ ሰሞናዊ ልምድ ፉርሽ ሆነ ። ለላፉት 162 ቀናት ፀንቶ የዘለቀው የሳሊባ እና ማጋሊሽ ተደናቂ የመድፉ ኮንክሪት ጥምረትን በአንድ ጀምበር ሄንካፔ እና ማስኬራ ሊወርሱ እንደማይችሉም ታየ ። ጠንቃቃው አርቴታም ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠ የሞየስስ ካይሲዶ ቀይ ካርድን ተከትሎ በደርቢው ቀን የተፈጠረለት ጨዋታውን የመቆጣጠር የማሸነፍ አጥቅቶ የመጫወት ሶስት ነጥብ ይዞ የመውጣት ዕድሉን አምክኖ ከምዕራብ ለንደን አንድ ነጥብ ይዞ ተመልሷል ። ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች ዋና የከተማ ባላንጣው አርሰናልን እንዳፈዘዘ ነጥብ ተጋርቶ ደርቢውን ፈፅሟል ። ጨዋታው የአርሰናል ደካማው የሲዝኑ አቋም ሆኗል ። 20 ዓመት ለተሻገረው የመድፉ የዋንጫ የተናፈቀ ህልም አርሰናል ከተራራው የስኬት ጫፍ ለመድረስ በገናናው ሊግ ኋያል የፉክክር ማዕበል ገና በአስደናቂ የቡድን መዋቅሩ ውስጥም አርሰናል በፈተናው እንደሚቀጥል የዛሬው የቼልሲ የለንደን ደርቢ ጨዋታ ማረጋገጫውን ሰጥቷል ።
በsuper sunday የሊጉ ሌሎች ጨዋታዎች የዩናይትድ ሄድ መለስ ቀጥሏል ። ከኤቨርተን ደካማ አቋም ማግስት ዩናይትድ ወደ ደቢብ ለንደን አቅንቶ ፓላስን 2ለ1 ረቷል ። ጨዋታውን በድል በመፈፀም ውስጥ ከሚገኝ ጠቀሜታ ባሻገር የአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጨዋታ ቀመርና የዩናይትድ ተጨዋቾች እንቅስቃሴ ዛሬም በትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደወደቀ ጨዋታው ተጠናቋል ።
ከተደራራቢ ሽንፈት የውጤት ቀውስ ጋር በተያያዘ ጨንቆት የከረመው ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ዌስትሃምን 2ለ0 ረቶ መጠነኛ ዕፎይታ አግኝቷል ። 130 ሚሊዮን ፓውንድ ያስወጣው አሌክሳንደር ኢሳክም የመጀመሪያውን ጎሉን በሊጉ አስቆጥሯል ። አሰልጣኝ አርን ስሎት ከኤልዛቤት ፓርክ የቀዩ ምድር ዋና ኮኮብ ሞሃመድ ሳላህን ሙሉ የጨዋታ ጊዜ ተጠባባቂ ወንበር ላይ እንዳስቀመጡ የራቀቸውን ድል መዶሻው ዌስትሃም ላይ አስመዝግበዋል
Tribune sport
ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች
#ethiopia | ማይክ አርቴታ ከደርቢው ጨዋታ አንድ ነጥብ ለመጋራት ብሪጅ የደረሰ መሰለ ። ከ55 ደቂቃዎች በላይ የነበረውን የተጨዋች ብልጫ አድቫንቴጅ ተከትሎ የተፈጠረለትን ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ አጋጣሚ አመከነ ። የመድፉ አለቃ ማይክ አርቴታ ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠም ፈፀመ ። አርሰናል ከቼልሲ 10 ኮኮቦች ፊት የነበረው የተቀዛቀዘ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጨዋታ ሜንታሊቲና ፍላጎት ብዙዎችን እንዳነገጋረ ለንደን ደርቢን በአቻ ውጤት ፈፅሟል ።
ከዋና ኮኮቡ ካይሲዶ ቀይ ካርድ በኋላ ሚስተር ቼልሲ በጨዋታው ይቸገራል ሲባል ጭራሽ አንሰራራ ። ከቀይ ካርዱ በኋላ የማሬስካ የጨዋታ ቀመር ከመድፉ ፊት የተሳካ ሆነ ። ከዕረፍት መልስ ቼልሲ 1ለዐ በቻሎባ ጎል ቀድሞም መራ ። ከአምበሉ ኦዴጋርድ ቅያሪ ተፅእኖ ጋር አርሰናል 1ለ0 የተመራውን ጨዋታ ወደ አንድ አቻ ውጤት በሜሬኖ ጎል በብርሃን ፍጥነት ቀየረ ። መድፉ የአቻዋን ጎል ተከትሎ በዛው የጀመረውን የማጥቃት ቴምፖ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲባል ግን መልሶ በጨዋታው ከማሬስካ ተደናቂ ጨዋታን የማስተዳደር ታክቲካል ማስተር Class አቅም ጋር ደበዘዘ ። የቼልሲ ኮኮቦች ውጤቱን ይዞ ለመውጣት የነበራቸው የተሳካ የደርቢው ፍጥጫ Dark Art እንቅስቃሴ ውስጥ አርሰናል እንደተመሰጠ ቀረ ።
ከጨዋታው ጅማሮ አንስቶ በፀብ አጫሪ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ እንቅስቃሴ ዝግጁነት መድፈኛውን በደርቢው ቀን በብሪጅ ያስተናገደው ቼልሲ የገጠመውን የካይሲዶ ቀይ ካርድ ተከትሎ በ10 ተጨዋች ሳይቸገር የተሻለም ተንቀሳቅሶ መደፈኛውን አፈዘዘ ። ቼልሲ አርሰናል የሲዝኑ ውጤታማ አጀማመሩን ተከትሎ በአድናቆት ቃላት አጀብ ብቻ የቆየው የሊጉ መሪ መድፈኞች እስካሁን ያልታዩ ሰፊ የቡድን ክፍተቶችን አንፀባረቀ ። አርሰናል ያለ ዋና ዋና የተከላካይ መስመር ደጀኖቹ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ወትሮም እንደተጠበቀው ተቸገረ ። በዴክላን ራይስ ሕያው አስደናቂ ተጋድሎ ሰፊ ከላላ ተደርጎላቸውም ከቼልሲ የማጥቃት እንቅስቃሴ ፊት የሳሊባ እና ማጋሊሽ አልጋወራሾች ሲወከቡ አመሹ ። ግብ ጠባቂው ዴቪድ ሬያም ያለ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ያለ ስራ እንደተቀመጠ 90 ደቂቃውን የመጨረስ ሰሞናዊ ልምድ ፉርሽ ሆነ ። ለላፉት 162 ቀናት ፀንቶ የዘለቀው የሳሊባ እና ማጋሊሽ ተደናቂ የመድፉ ኮንክሪት ጥምረትን በአንድ ጀምበር ሄንካፔ እና ማስኬራ ሊወርሱ እንደማይችሉም ታየ ። ጠንቃቃው አርቴታም ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠ የሞየስስ ካይሲዶ ቀይ ካርድን ተከትሎ በደርቢው ቀን የተፈጠረለት ጨዋታውን የመቆጣጠር የማሸነፍ አጥቅቶ የመጫወት ሶስት ነጥብ ይዞ የመውጣት ዕድሉን አምክኖ ከምዕራብ ለንደን አንድ ነጥብ ይዞ ተመልሷል ። ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች ዋና የከተማ ባላንጣው አርሰናልን እንዳፈዘዘ ነጥብ ተጋርቶ ደርቢውን ፈፅሟል ። ጨዋታው የአርሰናል ደካማው የሲዝኑ አቋም ሆኗል ። 20 ዓመት ለተሻገረው የመድፉ የዋንጫ የተናፈቀ ህልም አርሰናል ከተራራው የስኬት ጫፍ ለመድረስ በገናናው ሊግ ኋያል የፉክክር ማዕበል ገና በአስደናቂ የቡድን መዋቅሩ ውስጥም አርሰናል በፈተናው እንደሚቀጥል የዛሬው የቼልሲ የለንደን ደርቢ ጨዋታ ማረጋገጫውን ሰጥቷል ።
በsuper sunday የሊጉ ሌሎች ጨዋታዎች የዩናይትድ ሄድ መለስ ቀጥሏል ። ከኤቨርተን ደካማ አቋም ማግስት ዩናይትድ ወደ ደቢብ ለንደን አቅንቶ ፓላስን 2ለ1 ረቷል ። ጨዋታውን በድል በመፈፀም ውስጥ ከሚገኝ ጠቀሜታ ባሻገር የአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጨዋታ ቀመርና የዩናይትድ ተጨዋቾች እንቅስቃሴ ዛሬም በትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደወደቀ ጨዋታው ተጠናቋል ።
ከተደራራቢ ሽንፈት የውጤት ቀውስ ጋር በተያያዘ ጨንቆት የከረመው ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ዌስትሃምን 2ለ0 ረቶ መጠነኛ ዕፎይታ አግኝቷል ። 130 ሚሊዮን ፓውንድ ያስወጣው አሌክሳንደር ኢሳክም የመጀመሪያውን ጎሉን በሊጉ አስቆጥሯል ። አሰልጣኝ አርን ስሎት ከኤልዛቤት ፓርክ የቀዩ ምድር ዋና ኮኮብ ሞሃመድ ሳላህን ሙሉ የጨዋታ ጊዜ ተጠባባቂ ወንበር ላይ እንዳስቀመጡ የራቀቸውን ድል መዶሻው ዌስትሃም ላይ አስመዝግበዋል
Tribune sport
8 months ago
መድፈኞቹ Vs
ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች
#ethiopia | ማይክ አርቴታ ከደርቢው ጨዋታ አንድ ነጥብ ለመጋራት ብሪጅ የደረሰ መሰለ ። ከ55 ደቂቃዎች በላይ የነበረውን የተጨዋች ብልጫ አድቫንቴጅ ተከትሎ የተፈጠረለትን ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ አጋጣሚ አመከነ ። የመድፉ አለቃ ማይክ አርቴታ ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠም ፈፀመ ። አርሰናል ከቼልሲ 10 ኮኮቦች ፊት የነበረው የተቀዛቀዘ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጨዋታ ሜንታሊቲና ፍላጎት ብዙዎችን እንዳነገጋረ ለንደን ደርቢን በአቻ ውጤት ፈፅሟል ።
ከዋና ኮኮቡ ካይሲዶ ቀይ ካርድ በኋላ ሚስተር ቼልሲ በጨዋታው ይቸገራል ሲባል ጭራሽ አንሰራራ ። ከቀይ ካርዱ በኋላ የማሬስካ የጨዋታ ቀመር ከመድፉ ፊት የተሳካ ሆነ ። ከዕረፍት መልስ ቼልሲ 1ለዐ በቻሎባ ጎል ቀድሞም መራ ። ከአምበሉ ኦዴጋርድ ቅያሪ ተፅእኖ ጋር አርሰናል 1ለ0 የተመራውን ጨዋታ ወደ አንድ አቻ ውጤት በሜሬኖ ጎል በብርሃን ፍጥነት ቀየረ ። መድፉ የአቻዋን ጎል ተከትሎ በዛው የጀመረውን የማጥቃት ቴምፖ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲባል ግን መልሶ በጨዋታው ከማሬስካ ተደናቂ ጨዋታን የማስተዳደር ታክቲካል ማስተር Class አቅም ጋር ደበዘዘ ። የቼልሲ ኮኮቦች ውጤቱን ይዞ ለመውጣት የነበራቸው የተሳካ የደርቢው ፍጥጫ Dark Art እንቅስቃሴ ውስጥ አርሰናል እንደተመሰጠ ቀረ ።
ከጨዋታው ጅማሮ አንስቶ በፀብ አጫሪ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ እንቅስቃሴ ዝግጁነት መድፈኛውን በደርቢው ቀን በብሪጅ ያስተናገደው ቼልሲ የገጠመውን የካይሲዶ ቀይ ካርድ ተከትሎ በ10 ተጨዋች ሳይቸገር የተሻለም ተንቀሳቅሶ መደፈኛውን አፈዘዘ ። ቼልሲ አርሰናል የሲዝኑ ውጤታማ አጀማመሩን ተከትሎ በአድናቆት ቃላት አጀብ ብቻ የቆየው የሊጉ መሪ መድፈኞች እስካሁን ያልታዩ ሰፊ የቡድን ክፍተቶችን አንፀባረቀ ። አርሰናል ያለ ዋና ዋና የተከላካይ መስመር ደጀኖቹ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ወትሮም እንደተጠበቀው ተቸገረ ። በዴክላን ራይስ ሕያው አስደናቂ ተጋድሎ ሰፊ ከላላ ተደርጎላቸውም ከቼልሲ የማጥቃት እንቅስቃሴ ፊት የሳሊባ እና ማጋሊሽ አልጋወራሾች ሲወከቡ አመሹ ። ግብ ጠባቂው ዴቪድ ሬያም ያለ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ያለ ስራ እንደተቀመጠ 90 ደቂቃውን የመጨረስ ሰሞናዊ ልምድ ፉርሽ ሆነ ። ለላፉት 162 ቀናት ፀንቶ የዘለቀው የሳሊባ እና ማጋሊሽ ተደናቂ የመድፉ ኮንክሪት ጥምረትን በአንድ ጀምበር ሄንካፔ እና ማስኬራ ሊወርሱ እንደማይችሉም ታየ ። ጠንቃቃው አርቴታም ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠ የሞየስስ ካይሲዶ ቀይ ካርድን ተከትሎ በደርቢው ቀን የተፈጠረለት ጨዋታውን የመቆጣጠር የማሸነፍ አጥቅቶ የመጫወት ሶስት ነጥብ ይዞ የመውጣት ዕድሉን አምክኖ ከምዕራብ ለንደን አንድ ነጥብ ይዞ ተመልሷል ። ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች ዋና የከተማ ባላንጣው አርሰናልን እንዳፈዘዘ ነጥብ ተጋርቶ ደርቢውን ፈፅሟል ። ጨዋታው የአርሰናል ደካማው የሲዝኑ አቋም ሆኗል ። 20 ዓመት ለተሻገረው የመድፉ የዋንጫ የተናፈቀ ህልም አርሰናል ከተራራው የስኬት ጫፍ ለመድረስ በገናናው ሊግ ኋያል የፉክክር ማዕበል ገና በአስደናቂ የቡድን መዋቅሩ ውስጥም አርሰናል በፈተናው እንደሚቀጥል የዛሬው የቼልሲ የለንደን ደርቢ ጨዋታ ማረጋገጫውን ሰጥቷል ።
በsuper sunday የሊጉ ሌሎች ጨዋታዎች የዩናይትድ ሄድ መለስ ቀጥሏል ። ከኤቨርተን ደካማ አቋም ማግስት ዩናይትድ ወደ ደቢብ ለንደን አቅንቶ ፓላስን 2ለ1 ረቷል ። ጨዋታውን በድል በመፈፀም ውስጥ ከሚገኝ ጠቀሜታ ባሻገር የአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጨዋታ ቀመርና የዩናይትድ ተጨዋቾች እንቅስቃሴ ዛሬም በትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደወደቀ ጨዋታው ተጠናቋል ።
ከተደራራቢ ሽንፈት የውጤት ቀውስ ጋር በተያያዘ ጨንቆት የከረመው ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ዌስትሃምን 2ለ0 ረቶ መጠነኛ ዕፎይታ አግኝቷል ። 130 ሚሊዮን ፓውንድ ያስወጣው አሌክሳንደር ኢሳክም የመጀመሪያውን ጎሉን በሊጉ አስቆጥሯል ። አሰልጣኝ አርን ስሎት ከኤልዛቤት ፓርክ የቀዩ ምድር ዋና ኮኮብ ሞሃመድ ሳላህን ሙሉ የጨዋታ ጊዜ ተጠባባቂ ወንበር ላይ እንዳስቀመጡ የራቀቸውን ድል መዶሻው ዌስትሃም ላይ አስመዝግበዋል
Tribune sport
ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች
#ethiopia | ማይክ አርቴታ ከደርቢው ጨዋታ አንድ ነጥብ ለመጋራት ብሪጅ የደረሰ መሰለ ። ከ55 ደቂቃዎች በላይ የነበረውን የተጨዋች ብልጫ አድቫንቴጅ ተከትሎ የተፈጠረለትን ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ አጋጣሚ አመከነ ። የመድፉ አለቃ ማይክ አርቴታ ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠም ፈፀመ ። አርሰናል ከቼልሲ 10 ኮኮቦች ፊት የነበረው የተቀዛቀዘ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጨዋታ ሜንታሊቲና ፍላጎት ብዙዎችን እንዳነገጋረ ለንደን ደርቢን በአቻ ውጤት ፈፅሟል ።
ከዋና ኮኮቡ ካይሲዶ ቀይ ካርድ በኋላ ሚስተር ቼልሲ በጨዋታው ይቸገራል ሲባል ጭራሽ አንሰራራ ። ከቀይ ካርዱ በኋላ የማሬስካ የጨዋታ ቀመር ከመድፉ ፊት የተሳካ ሆነ ። ከዕረፍት መልስ ቼልሲ 1ለዐ በቻሎባ ጎል ቀድሞም መራ ። ከአምበሉ ኦዴጋርድ ቅያሪ ተፅእኖ ጋር አርሰናል 1ለ0 የተመራውን ጨዋታ ወደ አንድ አቻ ውጤት በሜሬኖ ጎል በብርሃን ፍጥነት ቀየረ ። መድፉ የአቻዋን ጎል ተከትሎ በዛው የጀመረውን የማጥቃት ቴምፖ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲባል ግን መልሶ በጨዋታው ከማሬስካ ተደናቂ ጨዋታን የማስተዳደር ታክቲካል ማስተር Class አቅም ጋር ደበዘዘ ። የቼልሲ ኮኮቦች ውጤቱን ይዞ ለመውጣት የነበራቸው የተሳካ የደርቢው ፍጥጫ Dark Art እንቅስቃሴ ውስጥ አርሰናል እንደተመሰጠ ቀረ ።
ከጨዋታው ጅማሮ አንስቶ በፀብ አጫሪ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ እንቅስቃሴ ዝግጁነት መድፈኛውን በደርቢው ቀን በብሪጅ ያስተናገደው ቼልሲ የገጠመውን የካይሲዶ ቀይ ካርድ ተከትሎ በ10 ተጨዋች ሳይቸገር የተሻለም ተንቀሳቅሶ መደፈኛውን አፈዘዘ ። ቼልሲ አርሰናል የሲዝኑ ውጤታማ አጀማመሩን ተከትሎ በአድናቆት ቃላት አጀብ ብቻ የቆየው የሊጉ መሪ መድፈኞች እስካሁን ያልታዩ ሰፊ የቡድን ክፍተቶችን አንፀባረቀ ። አርሰናል ያለ ዋና ዋና የተከላካይ መስመር ደጀኖቹ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ወትሮም እንደተጠበቀው ተቸገረ ። በዴክላን ራይስ ሕያው አስደናቂ ተጋድሎ ሰፊ ከላላ ተደርጎላቸውም ከቼልሲ የማጥቃት እንቅስቃሴ ፊት የሳሊባ እና ማጋሊሽ አልጋወራሾች ሲወከቡ አመሹ ። ግብ ጠባቂው ዴቪድ ሬያም ያለ ሳሊባ እና ማጋሊሽ ያለ ስራ እንደተቀመጠ 90 ደቂቃውን የመጨረስ ሰሞናዊ ልምድ ፉርሽ ሆነ ። ለላፉት 162 ቀናት ፀንቶ የዘለቀው የሳሊባ እና ማጋሊሽ ተደናቂ የመድፉ ኮንክሪት ጥምረትን በአንድ ጀምበር ሄንካፔ እና ማስኬራ ሊወርሱ እንደማይችሉም ታየ ። ጠንቃቃው አርቴታም ከቼልሲ ኋይል የቀላቀለ የጨዋታ ስትራቴጂ ጋር እንደተመሰጠ የሞየስስ ካይሲዶ ቀይ ካርድን ተከትሎ በደርቢው ቀን የተፈጠረለት ጨዋታውን የመቆጣጠር የማሸነፍ አጥቅቶ የመጫወት ሶስት ነጥብ ይዞ የመውጣት ዕድሉን አምክኖ ከምዕራብ ለንደን አንድ ነጥብ ይዞ ተመልሷል ። ሚስተር ቼልሲ በ10 ተጨዋች ዋና የከተማ ባላንጣው አርሰናልን እንዳፈዘዘ ነጥብ ተጋርቶ ደርቢውን ፈፅሟል ። ጨዋታው የአርሰናል ደካማው የሲዝኑ አቋም ሆኗል ። 20 ዓመት ለተሻገረው የመድፉ የዋንጫ የተናፈቀ ህልም አርሰናል ከተራራው የስኬት ጫፍ ለመድረስ በገናናው ሊግ ኋያል የፉክክር ማዕበል ገና በአስደናቂ የቡድን መዋቅሩ ውስጥም አርሰናል በፈተናው እንደሚቀጥል የዛሬው የቼልሲ የለንደን ደርቢ ጨዋታ ማረጋገጫውን ሰጥቷል ።
በsuper sunday የሊጉ ሌሎች ጨዋታዎች የዩናይትድ ሄድ መለስ ቀጥሏል ። ከኤቨርተን ደካማ አቋም ማግስት ዩናይትድ ወደ ደቢብ ለንደን አቅንቶ ፓላስን 2ለ1 ረቷል ። ጨዋታውን በድል በመፈፀም ውስጥ ከሚገኝ ጠቀሜታ ባሻገር የአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጨዋታ ቀመርና የዩናይትድ ተጨዋቾች እንቅስቃሴ ዛሬም በትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደወደቀ ጨዋታው ተጠናቋል ።
ከተደራራቢ ሽንፈት የውጤት ቀውስ ጋር በተያያዘ ጨንቆት የከረመው ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ዌስትሃምን 2ለ0 ረቶ መጠነኛ ዕፎይታ አግኝቷል ። 130 ሚሊዮን ፓውንድ ያስወጣው አሌክሳንደር ኢሳክም የመጀመሪያውን ጎሉን በሊጉ አስቆጥሯል ። አሰልጣኝ አርን ስሎት ከኤልዛቤት ፓርክ የቀዩ ምድር ዋና ኮኮብ ሞሃመድ ሳላህን ሙሉ የጨዋታ ጊዜ ተጠባባቂ ወንበር ላይ እንዳስቀመጡ የራቀቸውን ድል መዶሻው ዌስትሃም ላይ አስመዝግበዋል
Tribune sport
Sponsored by
Surafel
10 months ago
ሃማስ ለሰላም እጆቹን በመዘርጋቱ ደስ ብሎናል !/ በርካታ ሃገራት /
በ1967 ግብፅ ጋዛን ለእስራኤል ጦር አስረከበች ። በኋላም የፍልስጤሞችን ጥያቄ አዳፍና በ1978 የካምፕ ዴቪድ ሥምምነትን ተፈራርረመች ። ይሄን ተከትሎ ነዉ ሐማስን ጨምሮ ለፍልስጤማውያን እንታገላለን ያሉ ታጣቂዎች መደራጀት የጀመሩት ።
በዚህ ሁኔታ ለወትሮም ግጭት ፣ ሰብአዊ ጥፋት እና ቁሳዊ ውድመት የማይለየው ብሎም ሰላም ብርቁ የሆነው የመካከለኛው ምስራቅ የነበረውን የግጭት ጥላቻ ታሪክ ያስቀጠለ ነገር ተከሰተ ።
ዕለቱ ቅዳሜ ነው ፤ በአብዛኞቹ ምዕራባዉያን ሃገራት በሽብርተኝነት የተፈረጀው የፍልስጥኤማዊያኑ ታጣቂ ቡድን ሃማስ በፍጹም ያልተጠበቀ እና ድንገተኛ ጥቃት በእስራኤል ላይ ብርቱ ጉዳት አደረሰ ።
ባለፉት ሁለት አመታትም ጋዛ እንዳልነበረች ሆናለች ፤ ሊባኖስ ቤይሩት የጋዛን መንገድ የተከተሉ መስሏል ፤ ሞት እና ውድመት እዚህም እዚያም ይሰማል ፤ ከኢራን ብሎም ከሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላ እና ከሁቲ አማጽያን ከኋላ እና ከፊት የሚሳኤል እና የሮኬት ዝናብ የሚዘንብባት እስራኤል በቆሰለች ቁጥር ቁጣዋ እያየለ የምትወስደው እርምጃም ሰላማዊን ከጦረኛ ሳይለይ እንዳነፈረ እነሆ በሁለተኛው አመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰላም አየር መንፈስ ጀመረ ።
ትራምፕ የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነትን ለማስቆም እቅዳቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ጎራ ለይተው በዋና ተዋናይነት ላይ የነበሩት ሀማስና እስራኤል በፕሬዚዳንት ትራምፕ እቅድ መስማማታቸውን የሚገልጽ መግለጫ አዉጥተዋል ።
ፓኪስታን፣ ዮርዳኖስ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ኢንዶኔዢያ፣ ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር እና ግብፅን ጨምሮ በርካታ የአለም ሀገራት ማክሰኞ እለት የትራምፕን እቅድ የሚደግፉ የጋራ መግለጫ አውጥተው ሰላምን ለማስፈን ከአሜሪካ እና ከሌሎች ጋር ገንቢ በሆነ መልኩ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የቱርክ ፕሬዘደንት ሔርዶጋን የሃማስን አዎንታዊ ምላሽ በደስታ እንደተቀበሉት ቡድኑ "ለሰላም ዝግጁ"በመሆኑ ደስ እንዳላቸው ገልፀዋል.
"ሃማሰ ለሰላም ዝግጁ መሆኑ ሰውነቱን ያሳየበት ነዉ ስለሆነም, በክልላችን ውስጥ ሰላምን በዘላቂ ለማግኘት አንድ የእድል መስኮት እናየዋለን ብለዋል ።
ሌላኛዋ የቀጠናዉ ቁልፍ ተጫዋች ግብፅ የሃማስ "አዎንታዊ ምላሽ " እንዳስደሰታት እና በጋዛ ውስጥ ቋሚ ሰላም ለማምጣት የፈረሰዉን ለመገንባት ከሌሎች አረብ ግዛቶች ጋር እንደምትሰራ ተናግራለች ።
ኳታር ሃማስ ለፕሬዚዳንት ትራምፕ እቅዶችና ስምምነቶች አንድ አካል ለመሆን በመፍቀዱ ደስተኛ መሆኗን በመግለፅ ደም አፋሳሽ ጦርነቶች ዉድመቶች የደረሱበትን ጋዛን ለመገንባት የበኩሌን እወጣለሁ ብላለች ።
ፓኪስታን ሃማስ ለ Trump ዕቅድ የሰጠው ምላሽ "ደስተኝነት ነን" ያለች ሲሆን
" የፍልስጤምን ረሀብና ዉድመት ከዚህ በኋላ መቀጠል የለበትም እናም እስራኤልም ለሰላሙ ተግባራዊ እርምጃዎች መዉሰድ መጀመር አለባት ብላለች ። ሌሎችንም ከሰላሳ በላይ ሀገራት ሃማስ የትራምፕን ሃሳብ በመቀበል ለመስማማት መፍቀዱን በመግለጫቸው እንደገለፁ ከአልጀዚራ ሮይተርስ ሲኤንኤን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
በ1967 ግብፅ ጋዛን ለእስራኤል ጦር አስረከበች ። በኋላም የፍልስጤሞችን ጥያቄ አዳፍና በ1978 የካምፕ ዴቪድ ሥምምነትን ተፈራርረመች ። ይሄን ተከትሎ ነዉ ሐማስን ጨምሮ ለፍልስጤማውያን እንታገላለን ያሉ ታጣቂዎች መደራጀት የጀመሩት ።
በዚህ ሁኔታ ለወትሮም ግጭት ፣ ሰብአዊ ጥፋት እና ቁሳዊ ውድመት የማይለየው ብሎም ሰላም ብርቁ የሆነው የመካከለኛው ምስራቅ የነበረውን የግጭት ጥላቻ ታሪክ ያስቀጠለ ነገር ተከሰተ ።
ዕለቱ ቅዳሜ ነው ፤ በአብዛኞቹ ምዕራባዉያን ሃገራት በሽብርተኝነት የተፈረጀው የፍልስጥኤማዊያኑ ታጣቂ ቡድን ሃማስ በፍጹም ያልተጠበቀ እና ድንገተኛ ጥቃት በእስራኤል ላይ ብርቱ ጉዳት አደረሰ ።
ባለፉት ሁለት አመታትም ጋዛ እንዳልነበረች ሆናለች ፤ ሊባኖስ ቤይሩት የጋዛን መንገድ የተከተሉ መስሏል ፤ ሞት እና ውድመት እዚህም እዚያም ይሰማል ፤ ከኢራን ብሎም ከሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላ እና ከሁቲ አማጽያን ከኋላ እና ከፊት የሚሳኤል እና የሮኬት ዝናብ የሚዘንብባት እስራኤል በቆሰለች ቁጥር ቁጣዋ እያየለ የምትወስደው እርምጃም ሰላማዊን ከጦረኛ ሳይለይ እንዳነፈረ እነሆ በሁለተኛው አመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰላም አየር መንፈስ ጀመረ ።
ትራምፕ የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነትን ለማስቆም እቅዳቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ጎራ ለይተው በዋና ተዋናይነት ላይ የነበሩት ሀማስና እስራኤል በፕሬዚዳንት ትራምፕ እቅድ መስማማታቸውን የሚገልጽ መግለጫ አዉጥተዋል ።
ፓኪስታን፣ ዮርዳኖስ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ኢንዶኔዢያ፣ ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር እና ግብፅን ጨምሮ በርካታ የአለም ሀገራት ማክሰኞ እለት የትራምፕን እቅድ የሚደግፉ የጋራ መግለጫ አውጥተው ሰላምን ለማስፈን ከአሜሪካ እና ከሌሎች ጋር ገንቢ በሆነ መልኩ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የቱርክ ፕሬዘደንት ሔርዶጋን የሃማስን አዎንታዊ ምላሽ በደስታ እንደተቀበሉት ቡድኑ "ለሰላም ዝግጁ"በመሆኑ ደስ እንዳላቸው ገልፀዋል.
"ሃማሰ ለሰላም ዝግጁ መሆኑ ሰውነቱን ያሳየበት ነዉ ስለሆነም, በክልላችን ውስጥ ሰላምን በዘላቂ ለማግኘት አንድ የእድል መስኮት እናየዋለን ብለዋል ።
ሌላኛዋ የቀጠናዉ ቁልፍ ተጫዋች ግብፅ የሃማስ "አዎንታዊ ምላሽ " እንዳስደሰታት እና በጋዛ ውስጥ ቋሚ ሰላም ለማምጣት የፈረሰዉን ለመገንባት ከሌሎች አረብ ግዛቶች ጋር እንደምትሰራ ተናግራለች ።
ኳታር ሃማስ ለፕሬዚዳንት ትራምፕ እቅዶችና ስምምነቶች አንድ አካል ለመሆን በመፍቀዱ ደስተኛ መሆኗን በመግለፅ ደም አፋሳሽ ጦርነቶች ዉድመቶች የደረሱበትን ጋዛን ለመገንባት የበኩሌን እወጣለሁ ብላለች ።
ፓኪስታን ሃማስ ለ Trump ዕቅድ የሰጠው ምላሽ "ደስተኝነት ነን" ያለች ሲሆን
" የፍልስጤምን ረሀብና ዉድመት ከዚህ በኋላ መቀጠል የለበትም እናም እስራኤልም ለሰላሙ ተግባራዊ እርምጃዎች መዉሰድ መጀመር አለባት ብላለች ። ሌሎችንም ከሰላሳ በላይ ሀገራት ሃማስ የትራምፕን ሃሳብ በመቀበል ለመስማማት መፍቀዱን በመግለጫቸው እንደገለፁ ከአልጀዚራ ሮይተርስ ሲኤንኤን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
12 months ago
ይሄ ጠለፋ ሳይሆን የአንድ ሰው የፍቅር ታሪክ ነው::
ታሪክ የቀየረችው የኤዜ የስልክ ጥሪ
#ethiopia | አርሰናል ድምጹን አጥፍቶ ከፈጸማቸው ትልልቅ ዝውውሮች ምን አልባትም ይሄኛው ቀዳሚ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ኤቤሬቺ ኤዜ ከክሪስታል ፓላስ ወደ አርሰናል ያመራበት፡፡
እንግሊዛዊው ሁለ ገብ ተጫዋች በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር ስሙ ከአርሰናል ጋር ሲያያዝ ቢቆይም በመድፈኞቹ በኩል ያለው ፍላጎት እየቀዘቀዘ መምጣቱን ተከትሎ ቶተንሀም ዝውውሩን ገፍቶበታል፡፡
እዚህ ላይ ግን አንድ ነገር ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ ከሰኔ ወር ጀምሮ ከኤዜ ጋር በቅርበት በዝውውሩ ጉዳይ ሲያወራ ቆይቷል፡፡ የለንደን ተወላጁ ኤቤሪቺ ኤዜ እግር ኳስን የጀመረው በአርሰናል ቤት ነው፡፡ ለዚህ ክለብ የተለየ ፍቅር እንዳለው በተደጋጋሚ ሲናገር ይሰማል፡፡ ይሄንኑም ለክለቡ ያለውን ክብር ለሚካኤል አርቴታ ሲያስረዳም ቆይቷል፡፡
ኤቤሬቺ ኤዜ እግር ኳስን በአርሰናል አካዳሚ ቢጀምርም የ13 አመት ልጅ እያለ የአካዳሚው መልማዮች በወቅቱ ከእሱ የተሻሉ ታዳጊዎችን በማግኝታቸው እንዲቀነስ ሆነ፡፡ የለንደን ተወላጁ የያኔው ታዳጊ አርሰናልን እየወደደውም ቢሆን ለመለየት ተገደደ፡፡ በዚሁ ምክንያት ለተወሱኑ ቀናቶች ድብርት ውስጥ ገብቶ እንደነበርም ተዘግቧል፡፡
ከዚህ በኋላ ራሱን ለማግኝት ፉልሀም፣ ሪዲንግ፣ ሚልዋል፣ ኩይንስ ፓርክ ሬንጀርስ እና ወይኮምብ ወንድረስ ከቋሚነት እስከ ውሰት ያሳለፈባቸው ክለቦች ሆኑ፡፡ 2020 ላይ ግን ክሪስታል ፓላስ ኤዜን ከኪው ፒ አር በቋሚነት አስፈረመው፡፡ በሌላኛው የለንደን ክለብም ኤቤሬቺ ኤዜ ምርጥ መሆኑን አስመሰከረ፡፡
ሁለገቡ ተጫዋች በፓላስ ባሳየው ድንቅ ብቃት የበርካታ ክለቦች ትኩረት ሆነ፡፡ የእሱ ፍላጎት ግን በአውሮፓ ሻምፒንስ ሊግ የሚሳተፍ ከምንም በላይ ደግሞ ከእግር ኳስ ጋር የተዋወቀበት የልጅነት ክለቡ አርሰናል ነው፡፡ የአርሰናል ዝውውር ካልተሳካ የአርሰናል የምንጊዜም ተቀናቃኝ ወደ ሆነው ቶተንሀም ማምራት 2ኛ እቅዱም ሆነ፡፡
የቶተንሀሙ አማካይ ጄምስ ማዲሰን የጉልበት ጅማት መበጠስ ጉዳት ማስተናገዱ አሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ ኤዜን ብቸኛ አማራጭ አድርገው ወስደዋል፡፡
አርሰናል ኤዜ ላይ ያለው ፍላጎት በተጠበቀው ልክ አለመሄዱን ተከትሎ በክሪስታል ፓላስ እና በቶተንሀም መካከል ያለው ድርድር ከ90 በመቶ በላይ ተጠናቀቀ፡፡ የተጫዋቹም ወደ ነጭ ለባሾቹ ቤት የማምራት ዕድሉ በዚያው ልክ የተቃረበ ሆኗል፡፡
ከክለቦቹ ስምምነት በኋላ የ27 አመቱ ኤቤሬቺ ኤዜ ባለፈው ረቡ ፊርማውን ለቶተንሀም ለማስቀመጥ ቀጠሮ የያዘበት ዕለት ሆነ፡፡
ከዚህ በኋላ አንድ ነገር ተፈጠረ፡፡
ኤቤሬቺ ኤዜ ፊርማውን ለቶተንሀም ከማስቀመጡ በፊት የመጨረሻ እድሉን ለመሞከር ለአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ አንድ ስልክ ደወለ፡፡
“ለቶተንሀም ልፈርም ነው ወደ አርሰናል የምመጣበት ዕድል አብቅቷል ወይ የሚል መልዕክት ነበር”፡፡ ይቺ የመጨረሻ ስልክ ብዙ ነገሮችን የቀየረች እና ኤዜን ከልጅነት ክለቡ ጋር በድጋሜ እንዲገናኝ ትልቁን በር የከፈተች ሆነች፡፡
ሚካኤል አርቴታም የካይ ሀቨርዝን ጉዳት በተመለከተ ከቦርዱ ጋር ስብሰባ አድርጎ ስለበር በጀርመናዊው አጥቂ ቦታ ሌላ ሰው በማስፈለጉ ኤቤሬቺ ኤዜ በአርሰናል የሚፈለገው ሰው ሆነ፡፡
በሦስት ቦታ የሚጫወተው ኤዜም ለቶተንሀም የመፈረም ሃሳቡን በብርሀን ፍጥነት ቀይሮ ወደ አርሰናል ለማምራት ይሁንታውን ገለጸ፡፡ ረቡዕ ዕለት ለቶተንሀም ይፈርማል የተባለው ኤዜ የዚያኑ ቀን ሁሉንም ነገር ከአርሰናል ጋር ጨረሰ፡፡
ይሄ ዜና ከተሰማ በኋላ ወትሮም ከጎረቤታቸው አርሰናል ጋር በትልቅ ተቀናቃኝነት የሚተያዩት የቶተንሀም ደጋፊዎች እና የስራ ሃላፊዎች አስደንጋጩን ነገር ከመቀበል ውጭ አማራጭ አልነበራቸውም፡፡
የ27 አመቱ ኤዜም በድጋሜ ወደ አርሰናል ለመመለስ የመድፈኞቹ ተጫዋቾችን ጭምር ለማሳመን ያደረገው ጥረት ተሳክቶለት ከ14 አመታት በኋላ ወደ ኢምሬትስ ተመለሰ፡፡
የቶተንሀም ሰዎችን ጨምሮ ብዙዎች አርሰናል ተጫዋቹን ከቶተንሀም ሆትስፐር እንደ ጠለፈው ሊያስቡ ይችላሉ ነገር ግን ይሄ ኤቤሬቺ ኤዜ ለአርሰናል መለያ ያለውን ፍቅር እስከ መጨረሻው ሰአት ያሳየበት እና ያሳካበት የፍቅር ታሪክም ሆነ፡፡
ምሽት አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 5 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ከደጋፊዎቹ ጋር ሲተዋወቅ ፊቱ ላይ የሚታየውም ደስታ የዚሁ ማሳያ ነበር፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#arsenal #eze #ebcsport
ታሪክ የቀየረችው የኤዜ የስልክ ጥሪ
#ethiopia | አርሰናል ድምጹን አጥፍቶ ከፈጸማቸው ትልልቅ ዝውውሮች ምን አልባትም ይሄኛው ቀዳሚ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ኤቤሬቺ ኤዜ ከክሪስታል ፓላስ ወደ አርሰናል ያመራበት፡፡
እንግሊዛዊው ሁለ ገብ ተጫዋች በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር ስሙ ከአርሰናል ጋር ሲያያዝ ቢቆይም በመድፈኞቹ በኩል ያለው ፍላጎት እየቀዘቀዘ መምጣቱን ተከትሎ ቶተንሀም ዝውውሩን ገፍቶበታል፡፡
እዚህ ላይ ግን አንድ ነገር ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ ከሰኔ ወር ጀምሮ ከኤዜ ጋር በቅርበት በዝውውሩ ጉዳይ ሲያወራ ቆይቷል፡፡ የለንደን ተወላጁ ኤቤሪቺ ኤዜ እግር ኳስን የጀመረው በአርሰናል ቤት ነው፡፡ ለዚህ ክለብ የተለየ ፍቅር እንዳለው በተደጋጋሚ ሲናገር ይሰማል፡፡ ይሄንኑም ለክለቡ ያለውን ክብር ለሚካኤል አርቴታ ሲያስረዳም ቆይቷል፡፡
ኤቤሬቺ ኤዜ እግር ኳስን በአርሰናል አካዳሚ ቢጀምርም የ13 አመት ልጅ እያለ የአካዳሚው መልማዮች በወቅቱ ከእሱ የተሻሉ ታዳጊዎችን በማግኝታቸው እንዲቀነስ ሆነ፡፡ የለንደን ተወላጁ የያኔው ታዳጊ አርሰናልን እየወደደውም ቢሆን ለመለየት ተገደደ፡፡ በዚሁ ምክንያት ለተወሱኑ ቀናቶች ድብርት ውስጥ ገብቶ እንደነበርም ተዘግቧል፡፡
ከዚህ በኋላ ራሱን ለማግኝት ፉልሀም፣ ሪዲንግ፣ ሚልዋል፣ ኩይንስ ፓርክ ሬንጀርስ እና ወይኮምብ ወንድረስ ከቋሚነት እስከ ውሰት ያሳለፈባቸው ክለቦች ሆኑ፡፡ 2020 ላይ ግን ክሪስታል ፓላስ ኤዜን ከኪው ፒ አር በቋሚነት አስፈረመው፡፡ በሌላኛው የለንደን ክለብም ኤቤሬቺ ኤዜ ምርጥ መሆኑን አስመሰከረ፡፡
ሁለገቡ ተጫዋች በፓላስ ባሳየው ድንቅ ብቃት የበርካታ ክለቦች ትኩረት ሆነ፡፡ የእሱ ፍላጎት ግን በአውሮፓ ሻምፒንስ ሊግ የሚሳተፍ ከምንም በላይ ደግሞ ከእግር ኳስ ጋር የተዋወቀበት የልጅነት ክለቡ አርሰናል ነው፡፡ የአርሰናል ዝውውር ካልተሳካ የአርሰናል የምንጊዜም ተቀናቃኝ ወደ ሆነው ቶተንሀም ማምራት 2ኛ እቅዱም ሆነ፡፡
የቶተንሀሙ አማካይ ጄምስ ማዲሰን የጉልበት ጅማት መበጠስ ጉዳት ማስተናገዱ አሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ ኤዜን ብቸኛ አማራጭ አድርገው ወስደዋል፡፡
አርሰናል ኤዜ ላይ ያለው ፍላጎት በተጠበቀው ልክ አለመሄዱን ተከትሎ በክሪስታል ፓላስ እና በቶተንሀም መካከል ያለው ድርድር ከ90 በመቶ በላይ ተጠናቀቀ፡፡ የተጫዋቹም ወደ ነጭ ለባሾቹ ቤት የማምራት ዕድሉ በዚያው ልክ የተቃረበ ሆኗል፡፡
ከክለቦቹ ስምምነት በኋላ የ27 አመቱ ኤቤሬቺ ኤዜ ባለፈው ረቡ ፊርማውን ለቶተንሀም ለማስቀመጥ ቀጠሮ የያዘበት ዕለት ሆነ፡፡
ከዚህ በኋላ አንድ ነገር ተፈጠረ፡፡
ኤቤሬቺ ኤዜ ፊርማውን ለቶተንሀም ከማስቀመጡ በፊት የመጨረሻ እድሉን ለመሞከር ለአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ አንድ ስልክ ደወለ፡፡
“ለቶተንሀም ልፈርም ነው ወደ አርሰናል የምመጣበት ዕድል አብቅቷል ወይ የሚል መልዕክት ነበር”፡፡ ይቺ የመጨረሻ ስልክ ብዙ ነገሮችን የቀየረች እና ኤዜን ከልጅነት ክለቡ ጋር በድጋሜ እንዲገናኝ ትልቁን በር የከፈተች ሆነች፡፡
ሚካኤል አርቴታም የካይ ሀቨርዝን ጉዳት በተመለከተ ከቦርዱ ጋር ስብሰባ አድርጎ ስለበር በጀርመናዊው አጥቂ ቦታ ሌላ ሰው በማስፈለጉ ኤቤሬቺ ኤዜ በአርሰናል የሚፈለገው ሰው ሆነ፡፡
በሦስት ቦታ የሚጫወተው ኤዜም ለቶተንሀም የመፈረም ሃሳቡን በብርሀን ፍጥነት ቀይሮ ወደ አርሰናል ለማምራት ይሁንታውን ገለጸ፡፡ ረቡዕ ዕለት ለቶተንሀም ይፈርማል የተባለው ኤዜ የዚያኑ ቀን ሁሉንም ነገር ከአርሰናል ጋር ጨረሰ፡፡
ይሄ ዜና ከተሰማ በኋላ ወትሮም ከጎረቤታቸው አርሰናል ጋር በትልቅ ተቀናቃኝነት የሚተያዩት የቶተንሀም ደጋፊዎች እና የስራ ሃላፊዎች አስደንጋጩን ነገር ከመቀበል ውጭ አማራጭ አልነበራቸውም፡፡
የ27 አመቱ ኤዜም በድጋሜ ወደ አርሰናል ለመመለስ የመድፈኞቹ ተጫዋቾችን ጭምር ለማሳመን ያደረገው ጥረት ተሳክቶለት ከ14 አመታት በኋላ ወደ ኢምሬትስ ተመለሰ፡፡
የቶተንሀም ሰዎችን ጨምሮ ብዙዎች አርሰናል ተጫዋቹን ከቶተንሀም ሆትስፐር እንደ ጠለፈው ሊያስቡ ይችላሉ ነገር ግን ይሄ ኤቤሬቺ ኤዜ ለአርሰናል መለያ ያለውን ፍቅር እስከ መጨረሻው ሰአት ያሳየበት እና ያሳካበት የፍቅር ታሪክም ሆነ፡፡
ምሽት አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 5 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ከደጋፊዎቹ ጋር ሲተዋወቅ ፊቱ ላይ የሚታየውም ደስታ የዚሁ ማሳያ ነበር፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#arsenal #eze #ebcsport
1 year ago
" ዝናብን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ወደሱ ፊትን አዙሮ በጸሎትና በምልጃ መለመን አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው "- ብፁዕነታቸው
📌በሰሜን ወሎ ዞን ለሚገኙ ምዕምናን ለ7 ቀናት የሚቆይ ፀለተ ምኅላ እንዲይዙ ታዘዋል።
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በዞኑ በተለይ ቆላማ በሆኑ ሁሉም በሚባሉ ወረዳዎች የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ሰብል እንዳልተዘራና አርሶ አደሩም አዝኖ እንደተቀመጠ ገልፀዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ምን አሉ ?
" ለወትሮው ከሚያዚያ ጀምሮ የሚዘሩ አዝርዕቶች ዘንድሮ በዝናብ እጥረት አዝርዕት አልተዘሩም ይባስ ብሎ በዚህ ክረምት የሚዘሩ እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ አተርና ጤፍ የመሳሰሉት ተዘርተው በቅለው የሚታዩበት ጊዜ ነበር።
አሁን የሚታዩ ምንም አይነት ቡቃያ የለም። በተለይ በጉባላፍቶ፣ ሀብሩ፣ በራያ እና አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ መጋቢት አካባቢ ያለን ነው የሚመስለው ምንም አይነት ቅጠል የለም መሬቱ ደርቆ ነው ያለው።
ዝናብን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ወደሱ ፊትን አዙሮ በጸሎትና በምልጃ መለመን አማራጭ የሌለው መፍትሄ በመሆኑ ከሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ኹሉም ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተክርስቲያን በመገኘት ምዕምናን ለ7 ቀናት የሚቆይ ምኅላ ፀሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈናል " ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቄት ወረዳ አደጋ መካላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ የሆኑትን አቶ አታለል አለሙን በዚሁ ጉዳይ አነጋግሯል።
በወረዳው ባሉ 34 ቀበሌዎች ውስጥ በ19ኙ ቆላማ ቀበሌዎች ከፍተኛ ዝናብ እጥረት መከሰቱን አቶ አታለል ተናግረዋል። ይህም በግብርና ስራው ላይ ጥላ አጥልቷል ነው ያሉት።
" በ15 ደጋማ ቀበሌዎችም አጥጋቢ ዝናብ እየዘነበ አይደለም እንዲህ አይነት ችግር ደግሞ ሰብሉ ቢበቅል እንኳን ተባይና የሰብል በሽታ እንዲከሰት ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር ትልቅ ስጋት ፈጥሯል " ሲሉ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በ11ዱ ወረዳዎች ከፍተኛ የዝናብ እጥረት መከሰቱን መረጃ እንዳላቸው የገለፁት አቶ አታለል ወትሮም ቢሆን አካባቢው የአፈር ለምነቱን ያጣ የምግብ ዋስትናውን ያላረጋገጠ ነው ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ለሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መካላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ይመር አለሙ የእጅ ስልክ ላይ ደጋግመን ብንደውልም ስልኩ ባለመነሳቱ የተነሳ ሀሳብ አስተያየታቸውን ማካተት አልቻልንም ሲል የዘገበው ቲክቫህ ነው::
📌በሰሜን ወሎ ዞን ለሚገኙ ምዕምናን ለ7 ቀናት የሚቆይ ፀለተ ምኅላ እንዲይዙ ታዘዋል።
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በዞኑ በተለይ ቆላማ በሆኑ ሁሉም በሚባሉ ወረዳዎች የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ሰብል እንዳልተዘራና አርሶ አደሩም አዝኖ እንደተቀመጠ ገልፀዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ምን አሉ ?
" ለወትሮው ከሚያዚያ ጀምሮ የሚዘሩ አዝርዕቶች ዘንድሮ በዝናብ እጥረት አዝርዕት አልተዘሩም ይባስ ብሎ በዚህ ክረምት የሚዘሩ እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ አተርና ጤፍ የመሳሰሉት ተዘርተው በቅለው የሚታዩበት ጊዜ ነበር።
አሁን የሚታዩ ምንም አይነት ቡቃያ የለም። በተለይ በጉባላፍቶ፣ ሀብሩ፣ በራያ እና አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ መጋቢት አካባቢ ያለን ነው የሚመስለው ምንም አይነት ቅጠል የለም መሬቱ ደርቆ ነው ያለው።
ዝናብን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ወደሱ ፊትን አዙሮ በጸሎትና በምልጃ መለመን አማራጭ የሌለው መፍትሄ በመሆኑ ከሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ኹሉም ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተክርስቲያን በመገኘት ምዕምናን ለ7 ቀናት የሚቆይ ምኅላ ፀሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈናል " ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቄት ወረዳ አደጋ መካላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ የሆኑትን አቶ አታለል አለሙን በዚሁ ጉዳይ አነጋግሯል።
በወረዳው ባሉ 34 ቀበሌዎች ውስጥ በ19ኙ ቆላማ ቀበሌዎች ከፍተኛ ዝናብ እጥረት መከሰቱን አቶ አታለል ተናግረዋል። ይህም በግብርና ስራው ላይ ጥላ አጥልቷል ነው ያሉት።
" በ15 ደጋማ ቀበሌዎችም አጥጋቢ ዝናብ እየዘነበ አይደለም እንዲህ አይነት ችግር ደግሞ ሰብሉ ቢበቅል እንኳን ተባይና የሰብል በሽታ እንዲከሰት ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር ትልቅ ስጋት ፈጥሯል " ሲሉ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በ11ዱ ወረዳዎች ከፍተኛ የዝናብ እጥረት መከሰቱን መረጃ እንዳላቸው የገለፁት አቶ አታለል ወትሮም ቢሆን አካባቢው የአፈር ለምነቱን ያጣ የምግብ ዋስትናውን ያላረጋገጠ ነው ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ለሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መካላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ይመር አለሙ የእጅ ስልክ ላይ ደጋግመን ብንደውልም ስልኩ ባለመነሳቱ የተነሳ ሀሳብ አስተያየታቸውን ማካተት አልቻልንም ሲል የዘገበው ቲክቫህ ነው::
1 year ago
የዶናልድ ትራምፕ ከተማ በጋዛ እና የአውሮፓ ህብረት ልዩ አቋም!
#ethiopia | አሜሪካ ለወትሮም ለእስራኤል የምትሰጠው ድጋፍ አልተቋረጠም፡፡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ለአፍታም ቢሆን ተኩስ አቁም ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም በተለይ አሜሪካ ጋዛን እንድትቆጣጠር ያመጡት እቅድ ቁጣ ቀስቅሷል፡፡
በየካቲት ወር ፕሬዚዳንቱ 2 ሚሊዮን ፍልስጤማውያንን ከጋዛ አስወጥቶ ወደ ግብጽ እና ጆርዳን በማስፈር ጋዛን በአሜሪካ ባለቤትነት እንደገና መልሶ የማልማት እቅድ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
በእቅዳቸው በጋዛ ሰውሰራሽ ደሴት፣ ወደቦች፣ ፋብሪካዎች እና አለም አቀፍ ቱሪዝምን የሚስብ ልማት ይከናወናል ብለው ነበር፡፡ ይህ የትራምፕ እቅድ ከብዙ አቅጣጫ ተቃውሞ ገጥሞት ነበር፡፡ የአረብ ሃገራት፣ በተለይ እቅዱ የሚነካቸው ግብፅ እና ጆርዳንን ጨምሮ ሌሎችም ህገወጥ ነው ብለው ተችተዋል፡፡
የአውሮፓ ህብረት ሃገራትም የፍልስጤማውያንን በርስታቸው የመኖር መብታቸውን ይነካል ብለው እቅዱን ተችተዋል፡፡ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እቅዱ የዘር ማጽዳት ወንጀል ነው ብለው ነበር፡፡
እንደ አስገድዶ ህዝብን የማስፈር ያሉ የአለም አቀፍ ህግ የሚከለክላቸውን ወንጀሎች ይጥሳል፣ ፍልስጤማውያንን የማፅዳት ተግባር ስለሆነ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፣ ቀጠናውን በተለይም ግብጽ እና ጆርዳንን ይረብሻል፣ እንዲሁም የእስራኤል እና ፍልስጤምን ታሪካዊ ችግር ይቀርፋል የተባለውን የሁለት ሃገርነት መፍትሄ ያበላሻል የሚሉት በትራምፕ ዕቅድ ላይ የተነሱ ዋነኞቹ ትችቶች ናቸው፡፡
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ኔታንያሁ የትራምፕን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ደግፈው የአፈጻጸም ዝርዝር እቅድ ሁሉ አጋርተው ነበር፡፡
#selamshowbiz
#ethiopia | አሜሪካ ለወትሮም ለእስራኤል የምትሰጠው ድጋፍ አልተቋረጠም፡፡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ለአፍታም ቢሆን ተኩስ አቁም ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም በተለይ አሜሪካ ጋዛን እንድትቆጣጠር ያመጡት እቅድ ቁጣ ቀስቅሷል፡፡
በየካቲት ወር ፕሬዚዳንቱ 2 ሚሊዮን ፍልስጤማውያንን ከጋዛ አስወጥቶ ወደ ግብጽ እና ጆርዳን በማስፈር ጋዛን በአሜሪካ ባለቤትነት እንደገና መልሶ የማልማት እቅድ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
በእቅዳቸው በጋዛ ሰውሰራሽ ደሴት፣ ወደቦች፣ ፋብሪካዎች እና አለም አቀፍ ቱሪዝምን የሚስብ ልማት ይከናወናል ብለው ነበር፡፡ ይህ የትራምፕ እቅድ ከብዙ አቅጣጫ ተቃውሞ ገጥሞት ነበር፡፡ የአረብ ሃገራት፣ በተለይ እቅዱ የሚነካቸው ግብፅ እና ጆርዳንን ጨምሮ ሌሎችም ህገወጥ ነው ብለው ተችተዋል፡፡
የአውሮፓ ህብረት ሃገራትም የፍልስጤማውያንን በርስታቸው የመኖር መብታቸውን ይነካል ብለው እቅዱን ተችተዋል፡፡ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እቅዱ የዘር ማጽዳት ወንጀል ነው ብለው ነበር፡፡
እንደ አስገድዶ ህዝብን የማስፈር ያሉ የአለም አቀፍ ህግ የሚከለክላቸውን ወንጀሎች ይጥሳል፣ ፍልስጤማውያንን የማፅዳት ተግባር ስለሆነ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፣ ቀጠናውን በተለይም ግብጽ እና ጆርዳንን ይረብሻል፣ እንዲሁም የእስራኤል እና ፍልስጤምን ታሪካዊ ችግር ይቀርፋል የተባለውን የሁለት ሃገርነት መፍትሄ ያበላሻል የሚሉት በትራምፕ ዕቅድ ላይ የተነሱ ዋነኞቹ ትችቶች ናቸው፡፡
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ኔታንያሁ የትራምፕን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ደግፈው የአፈጻጸም ዝርዝር እቅድ ሁሉ አጋርተው ነበር፡፡
#selamshowbiz
Sponsored by
Surafel
Comments