60 mins. ago
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት የትራምፕን የጦርነት ስልጣን ለመገደብ ድምፅ ሰጡ
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ የወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስዱ የሚያግድ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በየካቲት ወር የጀመረውን ጦርነት በአደባባይ በመቃወም አራት ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ፤ የውሳኔ ሃሳቡ በ2መቶ15 ለ 2መቶ8 ድምፅ ሊጸድቅ ችሏል።
ይህ የተወካዮች ምክር ቤት በትራምፕ የጦርነት ስልጣን ላይ ገደብ ለመጣል የሞከረው ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ተቺዎች ፕሬዝዳንቱ የኮንግረሱን ፈቃድ ሳያገኙ እርምጃ እየወሰዱ ነው በማለት ይወቅሳሉ።
የምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ አሁንም በሪፐብሊካኖች በሚመራው የአሜሪካ ሴኔት መፅደቅ ይኖርበታል፤ይሁን እንጂ ሴኔቱ ቢቀበለው እንኳ እርምጃው በኢራን ላይ የሚሰነዘረውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ለመግታት መቻሉ አጠራጣሪ ነው፡፡
ውሳኔው ከዚህ ቀደም ሰባት ጊዜ ሳይሳካ ቀርቶ ባለፈው ግንቦት ወር ሴኔቱ መሰል የውሳኔ ሃሳብን ያራመደ ቢሆንም እስካሁን ሙሉ ድምፅ ለመስጠት ወደ መድረክ አላመጣውም።
እሮብ ዕለት የተካሄደው ድምፅ በትራምፕ እና ሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ ያለውን ልዩነት የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ምልክት ነው ፡፡
ይህ የሆነው ደግሞ በኮንግረስ ውስጥ ባሉ ወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ምክንያት አስተዳደሩ ለፖለቲካ አጋሮቹ ሊመድበው የነበረውን የ1.8 ቢሊየን ዶላር "ፀረ-የጦር መሣሪያ ታጣቂነት" ፈንድ ዕቅዱን ለመሰረዝ በተገደደ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው።
በተወካዮች ምክር ቤት የሚገኙ ቶማስ ማሲ፣ ብሪያን ፊትዝፓትሪክ፣ ቶም ባሬት እና ዋረን ዴቪድሰን የተባሉ ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች ጋር በመተባበር ረቡዕ ዕለት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አሳልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን ተቃውመው የነበሩት የሜይን ግዛት ዲሞክራት ጃሬድ ጎልደን በዚህ ጊዜ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ከሚቺጋን የመጡት ሪፐብሊካን ቶም ባሬትበበኩላቸው "ጦርነት የሚያውጀው ኮንግረስ ብቻ ነው፤ ይህ ደግሞ በእርግጥ ልንጠብቀው የሚገባ ጉዳይ ነው" ብለዋል።
በዚህ ድምፅ አሰጣጥ ምክንያት ከትራምፕ ሊሰነዘርባቸው ስለሚችለው የአጸፋ እርምጃ ተጠይቀው ሲመልሱ፡ "ትክክል ነው ብዬ ላመንኩበት ነገር በህሊናዬ ነው ድምፅ የሰጠሁት እናም የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ" ብለዋል።
በተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ መሪ የሆኑት ዲሞክራቱ ግሬገሪ ሚክስ፣ የተሰጠውን ድምፅ "በፕሬዝዳንት ትራምፕ ህገ-ወጥ እና ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለ ባለው የኢራን ጦርነት ላይ የተሰነዘረ ጠንካራ የሁለቱ ፓርቲዎች ተግሳጽ እና ጦርነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማቆም የተነገደ የመጀመሪያው እርምጃ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
ሚክስ አክለውም ትራምፕ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንዲንር ከማድረጋቸው እና ለኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ የመፈለጉን ሂደት ይበልጥ አስቸጋሪ ከማድረጋቸው ባለፈ የጦርነቱን የተቀመጡ ግቦች ማሳካት አልቻሉም ብለዋል።
የውሳኔ ሃሳቡን በጋራ ያዘጋጁት ሚክስ "የዚህ ውሳኔ መጽደቅ ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ ነው ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሪፐብሊካኖች በመካከለኛው ምስራቅ ሌላ ማብቂያ የሌለው ጦርነት የማይፈልጉትን የመራጮቻቸውን ድምፅ እየሰሙ ነው" ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በየካቲት 28 በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው የሚታወቁ ሲሆን ኢራንም በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ለሚገኙ የአሜሪካ አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለአለም አቀፍ የመርከብ ትራንስፖርት ወሳኝ የውሃ መስመር የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በውጤታማነት ዘግታለች።
13 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ የኢራንን የበለጸገ ዩራኒየም "ሄዳ እንደምትወስድ" እና ከሀገሪቱ ጋር እየተደረገ ያለው ድርድር እጅግ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ በኦቫል ኦፊስ አሁን ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል፣ የኢራንን የበለጸገ ዩራኒየም በተመለከተ "መውሰድ እፈልጋለሁ" በማለት አቋማቸውን በድጋሚ አንጸባርቀዋል። ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም እና "መሳሪያ" ያላቸው አሜሪካ እና ቻይና ብቻ መሆናቸውን የጠቀሱት ትራምፕ፣ "ሄደን እንወስደዋለን" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
በተጨማሪም በዋይት ሃውስ መግለጫ የሰጡት ትራምፕ ከኢራን ጋር እየተካሄደ ያለው ድርድር "እጅግ በጥሩ ሁኔታ" እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል። ሊደረስ ስለሚታሰበው ስምምነት ሲያብራሩም፣ "ላይሳካም ይችላል፣ ማወቅ አይቻልም፤ ነገር ግን የሚሳካ ከሆነ በዚሁ የሳምንቱ መጨረሻ ሊሆን ይችላል" ብለዋል። "ከኢራን ጋር በሚደረግ ማንኛውም ድርድር ላይ ምንም ነገር ሊፈጠር ይችላል" ሲሉም ሁኔታው ተለዋዋጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ከቴህራን ጋር የመግባቢያ ስምምነት "እንደተፈረመ ወዲያውኑ" የሆርሙዝ ስትሬት የውሃ መስመር ዳግም ክፍት እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቃል ገብተዋል። "በፍጥነት ክፍት ይሆናል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የውሃ መስመሩን ዳግም የመክፈት ጉዳይ አሁን በሊባኖስ እየተካሄደ ካለው ግጭት ነጥለው ለማየት እየሞከሩ መሆኑን አስረድተዋል። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በደቡብ ሊባኖስ የሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ በታቀደው መሰረት እንደሚቀጥል ማስታወቃቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል ጦር በአካባቢው የሚያደርሰውን ከባድ ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።
ፕሬዝዳንቱ በኦቫል ኦፊስ አሁን ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል፣ የኢራንን የበለጸገ ዩራኒየም በተመለከተ "መውሰድ እፈልጋለሁ" በማለት አቋማቸውን በድጋሚ አንጸባርቀዋል። ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም እና "መሳሪያ" ያላቸው አሜሪካ እና ቻይና ብቻ መሆናቸውን የጠቀሱት ትራምፕ፣ "ሄደን እንወስደዋለን" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
በተጨማሪም በዋይት ሃውስ መግለጫ የሰጡት ትራምፕ ከኢራን ጋር እየተካሄደ ያለው ድርድር "እጅግ በጥሩ ሁኔታ" እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል። ሊደረስ ስለሚታሰበው ስምምነት ሲያብራሩም፣ "ላይሳካም ይችላል፣ ማወቅ አይቻልም፤ ነገር ግን የሚሳካ ከሆነ በዚሁ የሳምንቱ መጨረሻ ሊሆን ይችላል" ብለዋል። "ከኢራን ጋር በሚደረግ ማንኛውም ድርድር ላይ ምንም ነገር ሊፈጠር ይችላል" ሲሉም ሁኔታው ተለዋዋጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ከቴህራን ጋር የመግባቢያ ስምምነት "እንደተፈረመ ወዲያውኑ" የሆርሙዝ ስትሬት የውሃ መስመር ዳግም ክፍት እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቃል ገብተዋል። "በፍጥነት ክፍት ይሆናል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የውሃ መስመሩን ዳግም የመክፈት ጉዳይ አሁን በሊባኖስ እየተካሄደ ካለው ግጭት ነጥለው ለማየት እየሞከሩ መሆኑን አስረድተዋል። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በደቡብ ሊባኖስ የሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ በታቀደው መሰረት እንደሚቀጥል ማስታወቃቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል ጦር በአካባቢው የሚያደርሰውን ከባድ ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።
15 hours ago
#ethiopia | ይህ መከራ ... እየሰፋ ነው | ሳንጠፋፋ መፍትሔ እንፈልግ | ፋርማሲ ቤቶች ጥብቅ መመርያ ተሰጣቸው | የአሜሪካና ኢራን ድርድር
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
20 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ እያካሄዱት ያለው ጦርነት ገና "እንዳላበቃ" ገልጸው፣ ሆኖም ቴህራን በውጊያው በእጅጉ "መዳከሟን" አጥብቀው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሳወቁት ለሲኤንቢሲ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ ላይ ነው። በወቅቱ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በየሁለት ቀኑ አንዴ እንደሚነጋገሩ የገለጹት ኔታንያሁ፣ "አልፎ አልፎ በስልታዊ ጉዳዮች ላይ የሐሳብ ልዩነቶች ቢኖሩንም፣ ሁልጊዜም መፍትሔ ላይ እንደርሳለን" ሲሉ የሁለቱን አገራት የጠበቀ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት አብራርተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ኃይሎች አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በኢራን ውስጥ ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ወደፊት ስለሚወሰደው ከባድ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውሳኔ ሲያስረዱም፣ "በቀጠናው ያለውን ውጥረት ማባባስ አስፈላጊ መሆን አለመሆኑን እንዲሁም የሆርሙዝ ስትሬትን (የባህር በር) በወታደራዊ ኃይል ማስከፈት ይቻል እንደሆነ የመወሰኑን ስልጣን ለትራምፕ ትተነዋል" ሲሉ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የመሪነት ሚና በእስራኤል በኩል ተቀባይነት እንዳለው የሚያንጸባርቅ ሐሳብ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ኃይሎች አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በኢራን ውስጥ ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ወደፊት ስለሚወሰደው ከባድ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውሳኔ ሲያስረዱም፣ "በቀጠናው ያለውን ውጥረት ማባባስ አስፈላጊ መሆን አለመሆኑን እንዲሁም የሆርሙዝ ስትሬትን (የባህር በር) በወታደራዊ ኃይል ማስከፈት ይቻል እንደሆነ የመወሰኑን ስልጣን ለትራምፕ ትተነዋል" ሲሉ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የመሪነት ሚና በእስራኤል በኩል ተቀባይነት እንዳለው የሚያንጸባርቅ ሐሳብ ሰጥተዋል።
21 hours ago
ኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
zena_maezen
zena_maezenኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
zena_maezen
zena_maezenኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኩዌት መከላከያ ሚኒስቴር ከማለዳ ጀምሮ ከኢራን ተነስተው ወደ አገሪቱ የአየር ክልል የገቡ 13 ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን እና 17 ድሮኖችን በተሳካ ሁኔታ ማክሸፉን በይፋ አስታውቋል። ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባሰፈረው አስቸኳይ መረጃ መሠረት፣ እነዚህ የአየር ላይ መጥለፎች የተከናወኑት "በተለያዩ የመኖሪያ አካባቢዎች" ላይ በመሆኑ፣ በጥቃቱ ማክሸፍ ሒደት የተከሰከሱ የብረትና የተተኳሽ ፍርስራሾች በሰዎች መኖሪያ መንደሮች ላይ ወድቀዋል።
ይህ ክስተት በመካከለኛው ምስራቅ በፍጥነት እየተባባሰ የመጣውን ከባድ የጸጥታ ቀውስ እና በንጹሃን ዜጎች ሰላማዊ ሕይወት ላይ የተጋረጠውን ከፍተኛ አደጋ በተግባር የሚያሳይ እጅግ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል። ሚኒስቴሩ በፈነዱትና በወደቁት ፍርስራሾች ሳቢያ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት በማስጠንቀቅ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት ወደደረሰባቸው እና ፍርስራሽ ወደወደቀባቸው የጥቃት ቀጠናዎች በፍጹም እንዳይቀርቡ በጥብቅ አሳስቧል።
ይህ ክስተት በመካከለኛው ምስራቅ በፍጥነት እየተባባሰ የመጣውን ከባድ የጸጥታ ቀውስ እና በንጹሃን ዜጎች ሰላማዊ ሕይወት ላይ የተጋረጠውን ከፍተኛ አደጋ በተግባር የሚያሳይ እጅግ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል። ሚኒስቴሩ በፈነዱትና በወደቁት ፍርስራሾች ሳቢያ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት በማስጠንቀቅ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት ወደደረሰባቸው እና ፍርስራሽ ወደወደቀባቸው የጥቃት ቀጠናዎች በፍጹም እንዳይቀርቡ በጥብቅ አሳስቧል።
Sponsored by
Surafel
21 hours ago
ኢራን በኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት በርካቶች መጎዳታቸው ተገለጸ
የኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋረጣቸው ተገለጸ።
በኩዌት የአውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት የተፈጸመው ቴህራን እና ዋሺንግተን አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ሲሆን በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውም ተገልጿል።
ሁለት የኢራን ዜና ወኪሎች ቴህራን የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር ማቋረጧን ማክሰኞ ዕለት ዘግበዋል።
ትራምፕ ግን ዘገባውን አጣጥለው ንግግሮች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋል።
የኩዌት መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳዑድ አብዱላዚዝ አል ኦታእቢ “በርካታ ጥቃት ፈጻሚ ድሮኖች” የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃን ዒላማ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።
በጥቃቱ የመንገደኞች ማስተናገጃው ክፉኛ መጎዳቱን የገለጹ ሲሆን “በርካታ ሰዎችን” አቁስሏል ብለዋል።
የአውሮፕላን ማረፊያው በኢራን ጦርነት ምክንያት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ከሁለት ቀናት በፊት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የአሜሪካ ጦር ኢራን በኩዌት እና ባህሬን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ጠቅሶ በወታደራዊ ተቋማቷ ላይ የአጸፋ ምላሽ ድብደባ ማካሄዱን አስታውቋል።
የአሜሪካ ጦር አክሎም በኩዌት የሚገኙ የጦር ሰፈሮቹን ዒላማ ያደረጉ “በርካታ ድሮኖችን መትተን ጥለናል” ሲል አስታውቋል።
የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ በባህሬን የሚገኝ የአሜሪካ ባሕር ኃይል ዋና ማዘዣ እና ኩዌትን በስም ሳይጠቅስ ሌላ አገር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
አክሎም ጥቃቱን የፈጸመው የአሜሪካ ጦር የጣለውን እገዳ ለማለፍ እየተንቀሳቀሰች የነበረች ነዳጅ ጫን መርከብ ሞተር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎመሆኑን ጠቅሷል።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው “ከዚህ በፊት ለማንኛውም ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ የተለየ እና የከፋ እንደሚሆን ተናግረን በነበረው መሠረተ እረምጃውን ወስደናል” ብሏል።
BBC
የኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋረጣቸው ተገለጸ።
በኩዌት የአውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት የተፈጸመው ቴህራን እና ዋሺንግተን አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ሲሆን በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውም ተገልጿል።
ሁለት የኢራን ዜና ወኪሎች ቴህራን የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር ማቋረጧን ማክሰኞ ዕለት ዘግበዋል።
ትራምፕ ግን ዘገባውን አጣጥለው ንግግሮች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋል።
የኩዌት መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳዑድ አብዱላዚዝ አል ኦታእቢ “በርካታ ጥቃት ፈጻሚ ድሮኖች” የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃን ዒላማ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።
በጥቃቱ የመንገደኞች ማስተናገጃው ክፉኛ መጎዳቱን የገለጹ ሲሆን “በርካታ ሰዎችን” አቁስሏል ብለዋል።
የአውሮፕላን ማረፊያው በኢራን ጦርነት ምክንያት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ከሁለት ቀናት በፊት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የአሜሪካ ጦር ኢራን በኩዌት እና ባህሬን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ጠቅሶ በወታደራዊ ተቋማቷ ላይ የአጸፋ ምላሽ ድብደባ ማካሄዱን አስታውቋል።
የአሜሪካ ጦር አክሎም በኩዌት የሚገኙ የጦር ሰፈሮቹን ዒላማ ያደረጉ “በርካታ ድሮኖችን መትተን ጥለናል” ሲል አስታውቋል።
የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ በባህሬን የሚገኝ የአሜሪካ ባሕር ኃይል ዋና ማዘዣ እና ኩዌትን በስም ሳይጠቅስ ሌላ አገር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
አክሎም ጥቃቱን የፈጸመው የአሜሪካ ጦር የጣለውን እገዳ ለማለፍ እየተንቀሳቀሰች የነበረች ነዳጅ ጫን መርከብ ሞተር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎመሆኑን ጠቅሷል።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው “ከዚህ በፊት ለማንኛውም ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ የተለየ እና የከፋ እንደሚሆን ተናግረን በነበረው መሠረተ እረምጃውን ወስደናል” ብሏል።
BBC
22 hours ago
ኢራን የኩዌት አየር መንገድን በዚ መልኩ ነው ያወደመችው በዚህ ጥቃት 63 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት የደርሰባቸው ሲሆን የሞቾች ቁጥርም ከአንድ ሊበልጥ እንደሚችል እየተናገሩ ይገኛል"
Seledadotio
Seledadotio
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
⚡️ "የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ከባድ ጥቃት ሰነዘሩ"
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
አሜሪካና ኢራን ተጠቃቁ
አሜሪካ በኢራን ገ’ሽም(ቀሽም) ደሴት ላይ ጥቃት አደረሰች።
ቴህራን በበኩሏ ኩዌትን እና ባህሬንን በምላሹ ማጥቃቷን አሳውቃለች።
የአሜሪካ ጦር ራስን ለመከላከል የተሰነዘረ ጥቃት ነው ቢለውም ተኩስ አቁሙን ገደል የከተተ ዕርምጃ ነው በሚል ትችት ተሰዝሮበታል።
ኢራንም በሚሳዔል እና ሰው አልባ አውሮፕላን የአሜሪካን ዒላማዎች በኩዌትና ባህሬን መምታቷን ቀጥላለች።
ዋሽንግተን ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደች ቢሆንም የተኩስ አቁም ድርድሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ብላለች።
ጥቃቱን ያደረሰው የአሜሪካው ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም ) እንደሆነም ተረጋግጧል።
ዕዙ ሁለት በኩዌት ላይ እንዲሁም በባህሬን ላይ ሶስት ሚሳኤሎችን ቴህራን ብታስወነጭፍም ዒላማቸውን ሳይመቱ ወድቀዋል አሊያም አየር ላይ ከሽፈዋል በሚል ሀሳብ ሰጥቷል።
የኩዌት ጦር የአየር መከላከያ ስርዓቶች ሚሳዔሎችንና ድሮኖችን በማክሸፉ ስራ ላይ ተጠመጃለሁም ብሏል።
በባህሬንም ከፍተኛ የአደጋ መጥቷል ድምፅ ሰጪ ደውሎች ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ አድረዋል ።
አልጀዚራ እንዳስነበበው።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካ በኢራን ገ’ሽም(ቀሽም) ደሴት ላይ ጥቃት አደረሰች።
ቴህራን በበኩሏ ኩዌትን እና ባህሬንን በምላሹ ማጥቃቷን አሳውቃለች።
የአሜሪካ ጦር ራስን ለመከላከል የተሰነዘረ ጥቃት ነው ቢለውም ተኩስ አቁሙን ገደል የከተተ ዕርምጃ ነው በሚል ትችት ተሰዝሮበታል።
ኢራንም በሚሳዔል እና ሰው አልባ አውሮፕላን የአሜሪካን ዒላማዎች በኩዌትና ባህሬን መምታቷን ቀጥላለች።
ዋሽንግተን ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደች ቢሆንም የተኩስ አቁም ድርድሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ብላለች።
ጥቃቱን ያደረሰው የአሜሪካው ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም ) እንደሆነም ተረጋግጧል።
ዕዙ ሁለት በኩዌት ላይ እንዲሁም በባህሬን ላይ ሶስት ሚሳኤሎችን ቴህራን ብታስወነጭፍም ዒላማቸውን ሳይመቱ ወድቀዋል አሊያም አየር ላይ ከሽፈዋል በሚል ሀሳብ ሰጥቷል።
የኩዌት ጦር የአየር መከላከያ ስርዓቶች ሚሳዔሎችንና ድሮኖችን በማክሸፉ ስራ ላይ ተጠመጃለሁም ብሏል።
በባህሬንም ከፍተኛ የአደጋ መጥቷል ድምፅ ሰጪ ደውሎች ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ አድረዋል ።
አልጀዚራ እንዳስነበበው።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ወራትን ያስቆጠረውን ጦርነት ለማቆም ተጀምሮ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ድርድር ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ያለ ምንም መሻሻል መጓተቱን ተከትሎ፣ አሜሪካ እና ኢራን አዳዲስ ጥቃቶችን መለዋወጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ጦር በኢራን ላይ የራስ መከላከል ጥቃቶችን መፈጸሙን እና ወደ መርከቦች እንዲሁም የባህረ ሰላጤው ሀገራት የተተኮሱ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) በሆርሙዝ ስትሬት በምትገኘው ቄሽም ደሴት ላይ የፈጸመው ጥቃት፣ ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ለሞከረችው ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የኢራን ወታደራዊ የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ዒላማ የተደረገ ሲሆን፣ በሕጋዊ መንገድ ቀጠናውን እያቋረጡ በነበሩ የሲቪል መርከበኞች ላይ የተተኮሱ ሦስት ድሮኖችን አሜሪካ አክሽፋለች። በተጨማሪም ወደ ኩዌት የተተኮሱ ሁለት የኢራን ሚሳኤሎች መንገድ ላይ ሲከሽፉ፣ ወደ ባህሬን የተተኮሱ ሦስት ሚሳኤሎች ደግሞ በአሜሪካ እና በባህሬን የአየር መከላከያ ኃይሎች መክሸፋቸው ተገልጿል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በከፊል የመንግሥት የሆነው የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል እንደዘገበው፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በአሜሪካ እና በኢራን ኃይሎች መካከል የተካሄደውን የትጥቅ እና የተኩስ ልውውጥ ቅደም ተከተል የሚያብራራ መረጃ ይፋ አድርጓል።
እንደ አብዮታዊ ዘቡ መግለጫ፣ ግጭቱ የጀመረው የአሜሪካ ኃይሎች በሆርሙዝ ስትሬት አቅራቢያ በሚገኝ የኢራን የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት በመሰንዘር የሞተር ክፍሉን ባወደሙበት ወቅት ነው።
ይህንን ተከትሎም IRGC (የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ) በአንድ የአሜሪካ-እስራኤል መርከብ ላይ የባህር ኃይል ሚሳኤሎችን በመጠቀም ጥቃት ማድረሱን ገልጿል።
ከዚህ የኢራን እርምጃ በኋላ፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከቄሽም ደሴት በስተደቡብ በሚገኝ የIRGC የመገናኛ ማማ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የኢራን አብዮታዊ ዘብ አስታውቋል።
በመጨረሻም IRGC ይህንን የዋሽንግተን እርምጃ ለመበቀል ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም "በቀጠናው ከሚገኙት ሀገራት በአንዱ ውስጥ በሚገኝ" የአሜሪካ አየር ኃይል ሰፈር፣ የአሜሪካ አምስተኛ የባህር ኃይል ዋና መምሪያ እና የጦር ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
(ይህ ሰበር ዜና እንደመሆኑ መጠን፣ የተከሰቱትን ክስተቶች በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዳገኘን የምናቀርብ ይሆናል።)
እንደ አብዮታዊ ዘቡ መግለጫ፣ ግጭቱ የጀመረው የአሜሪካ ኃይሎች በሆርሙዝ ስትሬት አቅራቢያ በሚገኝ የኢራን የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት በመሰንዘር የሞተር ክፍሉን ባወደሙበት ወቅት ነው።
ይህንን ተከትሎም IRGC (የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ) በአንድ የአሜሪካ-እስራኤል መርከብ ላይ የባህር ኃይል ሚሳኤሎችን በመጠቀም ጥቃት ማድረሱን ገልጿል።
ከዚህ የኢራን እርምጃ በኋላ፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከቄሽም ደሴት በስተደቡብ በሚገኝ የIRGC የመገናኛ ማማ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የኢራን አብዮታዊ ዘብ አስታውቋል።
በመጨረሻም IRGC ይህንን የዋሽንግተን እርምጃ ለመበቀል ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም "በቀጠናው ከሚገኙት ሀገራት በአንዱ ውስጥ በሚገኝ" የአሜሪካ አየር ኃይል ሰፈር፣ የአሜሪካ አምስተኛ የባህር ኃይል ዋና መምሪያ እና የጦር ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
(ይህ ሰበር ዜና እንደመሆኑ መጠን፣ የተከሰቱትን ክስተቶች በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዳገኘን የምናቀርብ ይሆናል።)
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ጦር በመካከለኛው ምስራቅ የተሰነዘሩ በርካታ የኢራን ባሊስቲክ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን በተሳካ ሁኔታ ማክሸፉን እና በቄሽም ደሴት ላይ የራስን መከላከል የአየር ጥቃት መፈጸሙን የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ጁን 2 ቀን 2026 ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ኢራን ወደ ቀጠናው ጎረቤት አገራት በርካታ ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ያስወነጨፈች ቢሆንም፣ ሁሉም የታለሙበትን ግብ ሳይመቱ ቀርተዋል። ወደ ኩዌት የተተኮሱ ሁለት የኢራን ሚሳኤሎች ግባቸውን ሳይመቱ መንገድ ላይ የተከሰከሱ ሲሆን፣ ወደ ባህሬን የተተኮሱ ሦስት ሚሳኤሎች ደግሞ በአሜሪካ እና በባህሬን የአየር መከላከያ ኃይሎች አማካኝነት ወዲያውኑ በአየር ላይ እንዲከሽፉ ተደርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የCENTCOM ኃይሎች ኢራን በሕጋዊ መንገድ ቀጠናዊ ባህርን እያቋረጡ በነበሩ ሲቪል መርከበኞች ላይ የሰነዘረቻቸውን ሦስት የአጥፊ ድሮኖችን መትተው ጥለዋል። የአሜሪካ ጦር ለተሰነዘረበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት በቄሽም ደሴት ላይ በሚገኘው የኢራን ወታደራዊ የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ላይ የተመጣጠነ የአየር ጥቃት ፈጽሟል።
በዚህ የጋራ የመከላከል እርምጃ ወቅት በየትኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ላይ የደረሰ ጉዳት የሌለ ሲሆን፣ ማዕከላዊ ዕዙ በአሁኑ ወቅት እየተተገበረ ባለው የተኩስ አቁም ስምምነት ወቅት ሊሰነዘሩ የሚችሉ ያልተገቡ የኢራን ትንኮሳዎችን ለመመከት እና ለመከላከል ኃይሎቹ በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
ኢራን ወደ ቀጠናው ጎረቤት አገራት በርካታ ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ያስወነጨፈች ቢሆንም፣ ሁሉም የታለሙበትን ግብ ሳይመቱ ቀርተዋል። ወደ ኩዌት የተተኮሱ ሁለት የኢራን ሚሳኤሎች ግባቸውን ሳይመቱ መንገድ ላይ የተከሰከሱ ሲሆን፣ ወደ ባህሬን የተተኮሱ ሦስት ሚሳኤሎች ደግሞ በአሜሪካ እና በባህሬን የአየር መከላከያ ኃይሎች አማካኝነት ወዲያውኑ በአየር ላይ እንዲከሽፉ ተደርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የCENTCOM ኃይሎች ኢራን በሕጋዊ መንገድ ቀጠናዊ ባህርን እያቋረጡ በነበሩ ሲቪል መርከበኞች ላይ የሰነዘረቻቸውን ሦስት የአጥፊ ድሮኖችን መትተው ጥለዋል። የአሜሪካ ጦር ለተሰነዘረበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት በቄሽም ደሴት ላይ በሚገኘው የኢራን ወታደራዊ የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ላይ የተመጣጠነ የአየር ጥቃት ፈጽሟል።
በዚህ የጋራ የመከላከል እርምጃ ወቅት በየትኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ላይ የደረሰ ጉዳት የሌለ ሲሆን፣ ማዕከላዊ ዕዙ በአሁኑ ወቅት እየተተገበረ ባለው የተኩስ አቁም ስምምነት ወቅት ሊሰነዘሩ የሚችሉ ያልተገቡ የኢራን ትንኮሳዎችን ለመመከት እና ለመከላከል ኃይሎቹ በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
2 days ago
እስካሁን ያላባራው የአሜሪካ እና የኢራን ውዝግብ
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
2 days ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በቀጣይ ሳምንት ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ሊደረስ እንደሚችል ትራምፕ ተናገሩ
ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ለማራዘም እና የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመክፈት በቀጣይ ሳምንት ስምምነት ላይ እንደሚደረስ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናገሩ።
“አሁን ላይ ነገሮች በጣም ጥሩ ናቸው። ውስን ችግር ነበር፤ ነገር ግን እንዳያችሁት በፍጥነት ፈትቼዋለሁ” ሲሉ በስልክ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል።
ትራምፕ ችግር ብለው የጠቀሱት እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት ኢራንን ማስቆጣቱን ነው።
ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረስ እንዲያቆም ከአሜሪካ የቀረበለትን ሐሳብ መቀበሉን ሊባኖስ አስታውቃለች። እስራኤልም በሊባኖስ መዲና ቤሩት ጥቃት ላለመፈጸም መስማማቷም ተገልጿል።
ትራምፕ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ከሄዝቦላህ ተወካዮች ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰው “ተኩስ ለማቆም ተስማምተዋል” ብለዋል።
ትራምፕ “ሄዝቦላህን አትተኩሱ ብያቸዋለሁ። ቢቢ [ኔታንያሁ] እንዳይተኩስም ነግሬዋለሁ። ሁለቱም ተኩስ አቁመዋል” ሲሉም አክለዋል።
በቀጣይ ሳምንት የሆርሙዝ ወሽመጥ ይከፈታል ብለው እንደሚያምኑም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
BBC
ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ለማራዘም እና የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመክፈት በቀጣይ ሳምንት ስምምነት ላይ እንደሚደረስ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናገሩ።
“አሁን ላይ ነገሮች በጣም ጥሩ ናቸው። ውስን ችግር ነበር፤ ነገር ግን እንዳያችሁት በፍጥነት ፈትቼዋለሁ” ሲሉ በስልክ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል።
ትራምፕ ችግር ብለው የጠቀሱት እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት ኢራንን ማስቆጣቱን ነው።
ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረስ እንዲያቆም ከአሜሪካ የቀረበለትን ሐሳብ መቀበሉን ሊባኖስ አስታውቃለች። እስራኤልም በሊባኖስ መዲና ቤሩት ጥቃት ላለመፈጸም መስማማቷም ተገልጿል።
ትራምፕ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ከሄዝቦላህ ተወካዮች ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰው “ተኩስ ለማቆም ተስማምተዋል” ብለዋል።
ትራምፕ “ሄዝቦላህን አትተኩሱ ብያቸዋለሁ። ቢቢ [ኔታንያሁ] እንዳይተኩስም ነግሬዋለሁ። ሁለቱም ተኩስ አቁመዋል” ሲሉም አክለዋል።
በቀጣይ ሳምንት የሆርሙዝ ወሽመጥ ይከፈታል ብለው እንደሚያምኑም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
BBC
2 days ago
የኢራኑ ፕሬዚዳንት የስራ
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን ኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የ"አሜሪካ ንብረት በሆነች" እና የፓናማ ባንዲራን በምታውለበልበው ኤም ኤስ ሲ ሳሪስካ ቪ የዕቃ መጫኛ (ኮንቴይነር) መርከብ ላይ የክሩዝ ሚሳኤል ጥቃት መፈጸሙን ይፋ አድርጓል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ አብዮታዊ ዘቡ ይህንን ወታደራዊ እርምጃ የወሰደው በቅርቡ በኦማን የባህር ክልል አቅራቢያ በአንዲት የኢራን መርከብ ላይ ለተፈጸመው ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ እርምጃ ቀጠናዊ ውጥረቱን ይበልጥ እንዳያባብሰው ስጋት ፈጥሯል።
የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ላይ ንግድ ኦፕሬሽን (UKMTO) ሪፖርት
በተያያዘ ዜና፣ UKMTO (የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ላይ ንግድ ኦፕሬሽን) በባህረ ሰላጤው አካባቢ ስትጓዝ የነበረች አንዲት የዕቃ መጫኛ መርከብ ከኡም ቃስር በስተደቡብ ምስራቅ 40 የባህር ማይል (ወይም 74 ኪ.ሜ) ርቀት ላይ በተወነጨፈ መሳሪያ ኢላማ መደረጓን ቀደም ብሎ ሪፖርት ማድረጉ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ተቋሙ ጥቃት የተፈጸመባት መርከብ በእርግጥም 'MSC Sariska V' ስለመሆንዋ ወይም ስለሌላ መርከብ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫ የለም። ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች በቀጠናው በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ያለውን የጸጥታ ስጋት በድጋሚ አጉልቶ አሳይቷል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ አብዮታዊ ዘቡ ይህንን ወታደራዊ እርምጃ የወሰደው በቅርቡ በኦማን የባህር ክልል አቅራቢያ በአንዲት የኢራን መርከብ ላይ ለተፈጸመው ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ እርምጃ ቀጠናዊ ውጥረቱን ይበልጥ እንዳያባብሰው ስጋት ፈጥሯል።
የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ላይ ንግድ ኦፕሬሽን (UKMTO) ሪፖርት
በተያያዘ ዜና፣ UKMTO (የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ላይ ንግድ ኦፕሬሽን) በባህረ ሰላጤው አካባቢ ስትጓዝ የነበረች አንዲት የዕቃ መጫኛ መርከብ ከኡም ቃስር በስተደቡብ ምስራቅ 40 የባህር ማይል (ወይም 74 ኪ.ሜ) ርቀት ላይ በተወነጨፈ መሳሪያ ኢላማ መደረጓን ቀደም ብሎ ሪፖርት ማድረጉ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ተቋሙ ጥቃት የተፈጸመባት መርከብ በእርግጥም 'MSC Sariska V' ስለመሆንዋ ወይም ስለሌላ መርከብ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫ የለም። ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች በቀጠናው በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ያለውን የጸጥታ ስጋት በድጋሚ አጉልቶ አሳይቷል።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረው የዲፕሎማሲ ድርድር ቢቋረጥም ምንም እንደማይገዳቸው እና የነዳጅ ዋጋ ንረትም ፈጽሞ እንደማያሳስባቸው በአደባባይ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ገበያ በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ወድቋል። ከዋሽንግተን ዲሲ የወጡ ወቅታዊ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ ይህ አስተያየት ከተሰማበት ከጥቂት ደቂቃዎች ጀምሮ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከባድ ስጋት ተፈጥሯል።
ይህ አሳሳቢ ዜና መሰራጨት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የወደፊቱ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት በማሻቀብ አንድ በርሜል ከመቶ ዶላር በላይ የዋጋ ጣሪያን ጥሶ አልፏል። የዛሬው የገበያ ውሎ ሲጀመር ከዚህ ዋጋ በእጅጉ ያነሰ የነበረ ቢሆንም፣ የፖለቲካው ውጥረት እና የትራምፕ ግዴለሽነት የተሞላበት ንግግር የገበያውን መረጋጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ አናግቶታል።
ይባስ ብሎም በገበያው ውስጥ ያለውን አሳሳቢ የነዳጅ ክምችት እጥረት በቅርበት የሚከታተሉ አንድ የኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የአቅርቦት እጥረቱን ተከትሎ የአንድ በርሜል ነዳጅ ዋጋ እስከ መቶ ሃምሳ ወይም መቶ ስልሳ ዶላር ሊደርስ እንደሚችል አስደንጋጭ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል። ይህ ዓይነቱ አስፈሪ የዋጋ ንረት እውን ከሆነ፣ የትራንስፖርት እና የማምረቻ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የከፋ እና በቀላሉ ሊቀለበስ የማይችል የኢኮኖሚ ቀውስ እንደሚያስከትል የዘርፉ ባለሙያዎች አጥብቀው እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
ይህ አሳሳቢ ዜና መሰራጨት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የወደፊቱ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት በማሻቀብ አንድ በርሜል ከመቶ ዶላር በላይ የዋጋ ጣሪያን ጥሶ አልፏል። የዛሬው የገበያ ውሎ ሲጀመር ከዚህ ዋጋ በእጅጉ ያነሰ የነበረ ቢሆንም፣ የፖለቲካው ውጥረት እና የትራምፕ ግዴለሽነት የተሞላበት ንግግር የገበያውን መረጋጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ አናግቶታል።
ይባስ ብሎም በገበያው ውስጥ ያለውን አሳሳቢ የነዳጅ ክምችት እጥረት በቅርበት የሚከታተሉ አንድ የኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የአቅርቦት እጥረቱን ተከትሎ የአንድ በርሜል ነዳጅ ዋጋ እስከ መቶ ሃምሳ ወይም መቶ ስልሳ ዶላር ሊደርስ እንደሚችል አስደንጋጭ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል። ይህ ዓይነቱ አስፈሪ የዋጋ ንረት እውን ከሆነ፣ የትራንስፖርት እና የማምረቻ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የከፋ እና በቀላሉ ሊቀለበስ የማይችል የኢኮኖሚ ቀውስ እንደሚያስከትል የዘርፉ ባለሙያዎች አጥብቀው እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶናልድ ትራምፕ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ከሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ ጋር ስኬታማ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን እና በተኩስ አቁም ዙሪያ ስምምነት ላይ መደረሱን ባስታወቁበት በአሁኑ ወቅት፣ የመካከለኛው ምስራቅ የፖለቲካ ትኩሳት ይበልጥ አሳሳቢ ወደሆነ እና ግራ አጋቢ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ትራምፕ ከኔታንያሁ ጋር ባደረጉት "እጅግ ፍሬያማ" ባሉት ውይይት፣ ወደ ሊባኖስ ዋና ከተማ ቤሩት የሚገቡ ተጨማሪ የእስራኤል ወታደሮች እንደማይኖሩ እና በመንገድ ላይ የነበሩትም ወደኋላ እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል።
ከዚህም ባሻገር ትራምፕ ከሄዝቦላህ ጋር "በጣም ጥሩ" የሚባል የስልክ ልውውጥ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ ታጣቂ ቡድኑ ማናቸውንም የተኩስ ልውውጦች ለማቆም መስማማቱን አውጀዋል። በእሳቸው አባባል እስራኤል በሄዝቦላህ ላይ፣ ሄዝቦላህም በእስራኤል ላይ ምንም ዓይነት ጥቃት እንደማይፈጽሙ መግባባት ላይ ተደርሷል። ይሁን እንጂ ይህን የትራምፕን ድንገተኛ የሰላም ብስራት በተመለከተ እስካሁን ከእስራኤልም ሆነ ከሄዝቦላህ በኩል የተሰጠ ምንም ዓይነት ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ አስተያየት አለመኖሩ፣ የጉዳዩን እውነተኛነት እና በመሬት ላይ ያለውን ተፈጻሚነት ከባድ ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋል።
በሌላ በኩል ይህ የተኩስ አቁም ወሬ እየተናፈሰ ባለበት አውድ፣ የኢራን መንግስት የወሰደው ጠንካራ አቋም የቀጠናውን ውጥረት ሌላ መልክ ሰጥቶታል። የኢራን ጠቅላይ መሪ አማካሪ የሆኑት ሞህሰን ሬዛኢ፣ ሀገራቸው በዓለም የነዳጅ ማስተላለፊያ የደም ስር በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ላይ ያላትን ሙሉ ቁጥጥር በድጋሚ በማረጋገጥ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። አማካሪው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ የባህር ላይ እገዳው እንዲቀጥል እንደማይፈቅዱ እና በሊባኖስ ላይ የሚደረገው የውጥረት መባባስም ፈጽሞ ተቀባይነት እንደሌለው አሳስበዋል። የኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ የጦር ኃይሎች ትዕግስት ገደብ አለው ያሉት ሬዛኢ፣ የውጭ የንግድ እና ወታደራዊ መርከቦች በስልታዊ የውሃ መስመሩ ላይ የተቀመጡትን ህጎች የማያከብሩ ከሆነ ኢላማ እንደሚደረጉ ያሳለፍነው ቅዳሜ የተሰጠውን ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ዳግም አጠናክረውታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢራን ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ድርድር ለማቋረጥ እያሰበች ነው ለሚለው ዘገባ ዶናልድ ትራምፕ የሰጡት ምላሽ እጅግ ቀዝቃዛ እና ግዴለሽነት የተሞላበት ነበር። ትራምፕ ለሲኤንቢሲ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ከኢራን ጋር ያለው የዲፕሎማሲ ድርድር ቢቋረጥም ምንም እንደማይገዳቸው እና ጉዳዩ እንደማያሳስባቸው በግልጽ ተናግረዋል። አክለውም ከዚህ የቀጠናው ውጥረት ጋር ተያይዞ የነዳጅ ዋጋ ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት እንደሌላቸው በማስገንዘብ፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንደ ድንጋይ ቁልቁል እንደሚወርድ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል።
እነዚህ ያልተረጋገጡ የሰላም ስምምነቶች ተቋማዊ ወታደራዊ ዛቻዎች እና ቸልተኝነት የተሞላባቸው የኢኮኖሚ ግምቶች ፉክክር፣ ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ጥሎት ይገኛል። የፖለቲካው ሚዛን በማንኛውም ሰዓት ሊለወጥ በሚችልበት በዚህ ወቅት፣ የመካከለኛው ምስራቅ እጣ ፈንታ በቃላት ጦርነት እና በተግባራዊ እርምጃዎች መካከል ክፉኛ እየተወዛወዘ ነው።
ከዚህም ባሻገር ትራምፕ ከሄዝቦላህ ጋር "በጣም ጥሩ" የሚባል የስልክ ልውውጥ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ ታጣቂ ቡድኑ ማናቸውንም የተኩስ ልውውጦች ለማቆም መስማማቱን አውጀዋል። በእሳቸው አባባል እስራኤል በሄዝቦላህ ላይ፣ ሄዝቦላህም በእስራኤል ላይ ምንም ዓይነት ጥቃት እንደማይፈጽሙ መግባባት ላይ ተደርሷል። ይሁን እንጂ ይህን የትራምፕን ድንገተኛ የሰላም ብስራት በተመለከተ እስካሁን ከእስራኤልም ሆነ ከሄዝቦላህ በኩል የተሰጠ ምንም ዓይነት ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ አስተያየት አለመኖሩ፣ የጉዳዩን እውነተኛነት እና በመሬት ላይ ያለውን ተፈጻሚነት ከባድ ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋል።
በሌላ በኩል ይህ የተኩስ አቁም ወሬ እየተናፈሰ ባለበት አውድ፣ የኢራን መንግስት የወሰደው ጠንካራ አቋም የቀጠናውን ውጥረት ሌላ መልክ ሰጥቶታል። የኢራን ጠቅላይ መሪ አማካሪ የሆኑት ሞህሰን ሬዛኢ፣ ሀገራቸው በዓለም የነዳጅ ማስተላለፊያ የደም ስር በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ላይ ያላትን ሙሉ ቁጥጥር በድጋሚ በማረጋገጥ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። አማካሪው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ የባህር ላይ እገዳው እንዲቀጥል እንደማይፈቅዱ እና በሊባኖስ ላይ የሚደረገው የውጥረት መባባስም ፈጽሞ ተቀባይነት እንደሌለው አሳስበዋል። የኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ የጦር ኃይሎች ትዕግስት ገደብ አለው ያሉት ሬዛኢ፣ የውጭ የንግድ እና ወታደራዊ መርከቦች በስልታዊ የውሃ መስመሩ ላይ የተቀመጡትን ህጎች የማያከብሩ ከሆነ ኢላማ እንደሚደረጉ ያሳለፍነው ቅዳሜ የተሰጠውን ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ዳግም አጠናክረውታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢራን ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ድርድር ለማቋረጥ እያሰበች ነው ለሚለው ዘገባ ዶናልድ ትራምፕ የሰጡት ምላሽ እጅግ ቀዝቃዛ እና ግዴለሽነት የተሞላበት ነበር። ትራምፕ ለሲኤንቢሲ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ከኢራን ጋር ያለው የዲፕሎማሲ ድርድር ቢቋረጥም ምንም እንደማይገዳቸው እና ጉዳዩ እንደማያሳስባቸው በግልጽ ተናግረዋል። አክለውም ከዚህ የቀጠናው ውጥረት ጋር ተያይዞ የነዳጅ ዋጋ ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት እንደሌላቸው በማስገንዘብ፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የነዳጅ ዋጋ እንደ ድንጋይ ቁልቁል እንደሚወርድ ትንበያቸውን አስቀምጠዋል።
እነዚህ ያልተረጋገጡ የሰላም ስምምነቶች ተቋማዊ ወታደራዊ ዛቻዎች እና ቸልተኝነት የተሞላባቸው የኢኮኖሚ ግምቶች ፉክክር፣ ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ጥሎት ይገኛል። የፖለቲካው ሚዛን በማንኛውም ሰዓት ሊለወጥ በሚችልበት በዚህ ወቅት፣ የመካከለኛው ምስራቅ እጣ ፈንታ በቃላት ጦርነት እና በተግባራዊ እርምጃዎች መካከል ክፉኛ እየተወዛወዘ ነው።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢራን ከአሜሪካ ጋር የሚደረገውን ንግግር ማቋረጧን አስታወቀች፡፡ የኢራን መንግስት በአደራዳሪዎች አማካኝነት ከአሜሪካ ጋር የሚያርገውን ግንኙነት ከዛሬ ጀምሮ ማቋረጡን ገለፀ፡፡ የኢራን ዜና አገልግሎት የሆነው ታስኒም እንደዘገበው ይህንን ንግግር መልሶ ለማስቀጠልም ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል፡፡
እንደዘገባው ኢራን ይህንን እርምጃ ለመውሰድ ያስገደዳት ዋነኛው ነጥብ ከሊባኖስ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ የኢራን ባለስልጣናት ለዜና አውታሩ በሰጡት መግለጫ እስራኤል በአካባቢው እያደረገች ያለውን ወታደራዊ ጥቃት በቀጠለበት ወቅት ምንም አይነት ንግግር እንደማይኖር ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም በሊባኖስ ብቻም ሳይሆን በቀጠናው ውስጥ ያሉት ጥቃቶች በሙሉ መቆም እንዳለባቸው እንደቅድመ ሁኔታ አስቀምጠዋል፡፡
የኢራን መንግስት ይህንን ውሳኔውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ከአሜሪካም ሆነ ዋነኛ አደራዳሪ ከሆነችው ፓኪስታን እስካሁን የተባለ ነገር የለም፡፡ ነገር ግን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታኒያሁ በደቡባዊ ሊባኖስ በተለይም በቤይሩት በተመረጡ ኢላማዎች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
እንደዘገባው ኢራን ይህንን እርምጃ ለመውሰድ ያስገደዳት ዋነኛው ነጥብ ከሊባኖስ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ የኢራን ባለስልጣናት ለዜና አውታሩ በሰጡት መግለጫ እስራኤል በአካባቢው እያደረገች ያለውን ወታደራዊ ጥቃት በቀጠለበት ወቅት ምንም አይነት ንግግር እንደማይኖር ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም በሊባኖስ ብቻም ሳይሆን በቀጠናው ውስጥ ያሉት ጥቃቶች በሙሉ መቆም እንዳለባቸው እንደቅድመ ሁኔታ አስቀምጠዋል፡፡
የኢራን መንግስት ይህንን ውሳኔውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ከአሜሪካም ሆነ ዋነኛ አደራዳሪ ከሆነችው ፓኪስታን እስካሁን የተባለ ነገር የለም፡፡ ነገር ግን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታኒያሁ በደቡባዊ ሊባኖስ በተለይም በቤይሩት በተመረጡ ኢላማዎች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ በሚካሄደው የዘንድሮው የጦር መሣሪያ እና መከላከያ አውደ ርዕይ ላይ እስራኤል እንዳትሳተፍ መታገዷን ተከትሎ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የዲፕሎማሲ ውጥረት ወደ አዲስ እና አሳሳቢ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ የፈረንሳይ ባለስልጣናት እስራኤል ብሔራዊ ድንኳን እንዳትተክል እና የመንግስት ተወካዮቿን ወደ ዝግጅቱ እንዳትልክ በይፋ ከልክለዋል። በዚህ ውሳኔ መሰረት፣ የፈረንሳይ መንግስት የእስራኤል የመከላከያ ኩባንያዎች የአየር መከላከያ ስርአቶችን ብቻ እንዲያሳዩ የፈቀደ ሲሆን፣ ማናቸውንም የማጥቃት አቅም ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች ማቅረብን ግን በጥብቅ አግዷል።
ይህንን ድርጊት ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ውሳኔውን "አሳፋሪ" ሲል አውግዞታል። ሚኒስቴሩ እርምጃው ከፖለቲካዊ እና የንግድ ስሌቶች የመነጨ መሆኑን በመግለጽ፣ ፈረንሳይ በሌሎች ተሳታፊ ሀገራት ላይ ያልተገበረችውን አድሏዊ ክልከላ በእስራኤል ላይ ብቻ መጫኗ ዓለም አቀፍ የአውደ ርዕይ ህጎችንና መርሆዎችን የጣሰ ነው ብሏል። ከዚህም ባሻገር፣ ፈረንሳይ ቆሜላቸዋለሁ ከምትላቸው መርሆች ጋር የሚጋጭ ድርጊት እየፈጸመች መሆኑን በመሞገት፣ የታገዱት የእስራኤል አጥቂ የጦር መሳሪያዎች ዓለም አቀፍ እና ቀጠናዊ መረጋጋትን በሚያናጉ አሸባሪ ቡድኖች እና መንግስታት ላይ ያላቸውን ውጤታማነት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አበክሮ ተከራክሯል።
ይህ አሳሳቢ ክልከላ የመጣው በእየሩሳሌም እና በፓሪስ መካከል ያለው የፖለቲካ ትኩሳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመጣበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ሚያዝያ ወር፣ ፈረንሳይ የእስራኤል አውሮፕላኖች ከኢራን ጋር ለነበረው ውጊያ የፈረንሳይን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ መከልከሏን ተከትሎ፣ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ከፈረንሳይ የሚያደርገውን ማናቸውንም የጦር መሳሪያ ግዢ ማቋረጡ ይታወሳል። ይህ እርምጃ የእስራኤልን ደህንነት የሚጎዳ ነው በሚል የተወሰደ የቅጣት ምላሽ እንደነበር ሚኒስቴሩ በወቅቱ አሳውቆ ነበር።
የሁለቱ ሀገራት የጦር መሳሪያ አውደ ርዕይ ውዝግብ አዲስ ክስተት አይደለም።
የፈረንሳይ ባለስልጣናት ባለፈው የ2024 አውደ ርዕይ ላይ የእስራኤል ኩባንያዎች እንዳይሳተፉ መጀመሪያ ላይ አግደው በኋላ ላይ ውሳኔውን መቀልበሳቸው አይዘነጋም። እንዲሁም በ2025ቱ የፓሪስ የአየር ትርኢት ላይ አዘጋጆቹ የእስራኤል ኩባንያዎች አጥቂ መሳሪያዎችን በሚያሳዩባቸው ማሳያዎች ዙሪያ ጥቁር የከለላ ግድግዳዎችን በመገንባት ማግለላቸው የፈጠረው ቁርሾ አሁንም ድረስ አልበረደም። የዘንድሮው ሙሉ እገዳ ግን የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
ይህንን ድርጊት ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ውሳኔውን "አሳፋሪ" ሲል አውግዞታል። ሚኒስቴሩ እርምጃው ከፖለቲካዊ እና የንግድ ስሌቶች የመነጨ መሆኑን በመግለጽ፣ ፈረንሳይ በሌሎች ተሳታፊ ሀገራት ላይ ያልተገበረችውን አድሏዊ ክልከላ በእስራኤል ላይ ብቻ መጫኗ ዓለም አቀፍ የአውደ ርዕይ ህጎችንና መርሆዎችን የጣሰ ነው ብሏል። ከዚህም ባሻገር፣ ፈረንሳይ ቆሜላቸዋለሁ ከምትላቸው መርሆች ጋር የሚጋጭ ድርጊት እየፈጸመች መሆኑን በመሞገት፣ የታገዱት የእስራኤል አጥቂ የጦር መሳሪያዎች ዓለም አቀፍ እና ቀጠናዊ መረጋጋትን በሚያናጉ አሸባሪ ቡድኖች እና መንግስታት ላይ ያላቸውን ውጤታማነት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አበክሮ ተከራክሯል።
ይህ አሳሳቢ ክልከላ የመጣው በእየሩሳሌም እና በፓሪስ መካከል ያለው የፖለቲካ ትኩሳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመጣበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ሚያዝያ ወር፣ ፈረንሳይ የእስራኤል አውሮፕላኖች ከኢራን ጋር ለነበረው ውጊያ የፈረንሳይን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ መከልከሏን ተከትሎ፣ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ከፈረንሳይ የሚያደርገውን ማናቸውንም የጦር መሳሪያ ግዢ ማቋረጡ ይታወሳል። ይህ እርምጃ የእስራኤልን ደህንነት የሚጎዳ ነው በሚል የተወሰደ የቅጣት ምላሽ እንደነበር ሚኒስቴሩ በወቅቱ አሳውቆ ነበር።
የሁለቱ ሀገራት የጦር መሳሪያ አውደ ርዕይ ውዝግብ አዲስ ክስተት አይደለም።
የፈረንሳይ ባለስልጣናት ባለፈው የ2024 አውደ ርዕይ ላይ የእስራኤል ኩባንያዎች እንዳይሳተፉ መጀመሪያ ላይ አግደው በኋላ ላይ ውሳኔውን መቀልበሳቸው አይዘነጋም። እንዲሁም በ2025ቱ የፓሪስ የአየር ትርኢት ላይ አዘጋጆቹ የእስራኤል ኩባንያዎች አጥቂ መሳሪያዎችን በሚያሳዩባቸው ማሳያዎች ዙሪያ ጥቁር የከለላ ግድግዳዎችን በመገንባት ማግለላቸው የፈጠረው ቁርሾ አሁንም ድረስ አልበረደም። የዘንድሮው ሙሉ እገዳ ግን የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን መንግስታዊ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሰሜናዊ ኢራቅ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ታጣቂ እና ተገንጣይ ቡድኖች የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ፈጽሟል።
መገናኛ ብዙሃኑ ይህ ወታደራዊ ዘመቻ የተካሄደው በአብዮታዊ ዘቡ የምድር ጦር መሆኑን ቢገልጹም፣ ጥቃቱ የተሰነዘረባቸውን የተወሰኑ ቡድኖች ማንነትም ሆነ የተመቱትን አካባቢዎች ዝርዝር መረጃ አላቀረቡም።
ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
መገናኛ ብዙሃኑ ይህ ወታደራዊ ዘመቻ የተካሄደው በአብዮታዊ ዘቡ የምድር ጦር መሆኑን ቢገልጹም፣ ጥቃቱ የተሰነዘረባቸውን የተወሰኑ ቡድኖች ማንነትም ሆነ የተመቱትን አካባቢዎች ዝርዝር መረጃ አላቀረቡም።
ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደራደሩባቸው ነጥቦች የበለጠ እንዲጠናከሩ መጠየቃቸው ተዘገበ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኳታር መንግስት ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ቻርተር ያለውን ሙሉ ቁርጠኝነት በማረጋገጥ፣ በቻርተሩ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ተደጋጋሚ ጥሰቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ አቀረበ። ኳታር በተመድ ማዕከልነት እና በቻርተሩ ላይ የተመሰረተውን ዓለም አቀፍ ስርዓት ለማጠናከር የምታደርገውን ጥረት እንዲሁም ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቃለች።
ይህ የተገለጸው በኒውዮርክ የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት “የተመድ ቻርተርን ማክበር እና በተመድ ላይ የተመሰረተውን ዓለም አቀፍ ስርዓት ማጠናከር” በሚል ርዕስ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ ላይ፣ በተመድ የኳታር ቋሚ መልዕክተኛ በሆኑት ሼክ አሊያ አህመድ ቢን ሰይፍ አል-ታኒ አማካኝነት ነው። መልዕክተኛዋ በመግለጫቸው፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ የተመሰረተው የተመድ ቻርተር የህግ ሰነድ ብቻ ሳይሆን የጦርነትን አደጋ ለመከላከል ቃል የተገባበት የሞራል ስምምነት መሆኑን አስምረውበታል።
አክለውም አሁን ያለው በቻርተር ላይ የተመሰረተው ዓለም አቀፍ ስርዓት፣ የሀገራትን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በሚጥሱ አደገኛ ጥቃቶች ምክንያት ከዚህ ቀደም ታይቶ ለማይታወቅ ፈተና መጋለጡን ጠቁመዋል። እነዚህ ጥቃቶች የተመድን ተዓማኒነት የሚሸረሽሩ በመሆናቸው፣ ለቻርተሩ ቁርጠኛ የሆነ እና በተባበሩት መንግስታት በኩል ብዝሃነትን የሚያጠናክር እውነተኛ የፖለቲካ ፍላጎት ማምጣት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። አሁን ያሉትን ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎች ለመፍታት ከቻርተሩ አላማዎች እና ከተመድ ምስረታ ግቦች ጋር የሚጣጣም የጋራ ዓለም አቀፋዊ ምላሽ እንደሚያስፈልግም መልዕክተኛዋ አብራርተዋል።
በዚህ ረገድ ሼክ አሊያ የቻርተሩን መርሆዎች ሙሉ በሙሉ መተግበር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው፣ የቻርተሩን ድንጋጌዎች በሚተረጉሙበት ወቅት አድልዎ ከማድረግ መቆጠብ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም በሀገራት መካከል ያለውን የሉዓላዊነት እኩልነት መርህ በማጉላት፣ በተለይም አሁን ባለው የዓለም አቀፍ ህግ እና የዓለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ ግልጽ ጥሰቶች መሃል የኃይል እርምጃ መውሰድ ወይም በኃይል መዛት ሊከለከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የነባሩ ዓለም አቀፍ ስርዓት ዋነኛ ማዕቀፍ ሆኖ መቀጠሉ ወሳኝ መሆኑን ኳታር እንደምትገነዘብ ያነሱት መልዕክተኛዋ፣ ስርዓቱ የሃያ አንደኛውን ክፍለ ዘመን ተግዳሮቶች መቋቋም የሚችል፣ ሁሉን አቀፍ እና ውጤታማ እንዲሆን የተመድ ተቋማዊ ማሻሻያ በፍጥነት ሊተገበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ተቋሙ ተልዕኮውን በሚገባ እንዲወጣ በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል እና በተቋማዊ አቅም ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ግጭትን የመከላከል ስርዓት ላይ ኢንቨስት ማድረግ እና የግጭቶችን መንስኤዎች መፍታት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት መልዕክተኛዋ፣ ኳታር ሽምግልናን እና የመከላከያ ዲፕሎማሲን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ዋነኛ ምሰሶ አድርጋ እንደምትጠቀም አስታውሰዋል። ኳታር የተኩስ አቁም ስምምነቶችን፣ የፖለቲካ እስረኞች ልውውጥን፣ የግጭት አፈታት እና የሰላም ስምምነቶችን በተለያዩ አህጉራት በማመቻቸት የተመድ ስትራቴጂካዊ አጋር እና ታማኝ ዓለም አቀፍ አደራዳሪ መሆኗን አስመስክራለች ብለዋል።
የኳታር መንግስት በአሜሪካ እና በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መካከል ፓኪስታን እየመራች ላለው የሽምግልና ጥረት ምስጋናዋን እንደምታቀርብ እና ጥረቱንም እንደምትደግፍ አረጋግጠዋል። በቀጠናው ውጥረትን ለማርገብ፣ ሰላም እና መረጋጋትን ለማምጣት የሚያስችሉ እነዚህን የሽምግልና ጥረቶች ኳታር ሙሉ በሙሉ እንደምትደግፍም መልዕክተኛዋ አረጋግጠዋል።
ይህ የተገለጸው በኒውዮርክ የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት “የተመድ ቻርተርን ማክበር እና በተመድ ላይ የተመሰረተውን ዓለም አቀፍ ስርዓት ማጠናከር” በሚል ርዕስ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ ላይ፣ በተመድ የኳታር ቋሚ መልዕክተኛ በሆኑት ሼክ አሊያ አህመድ ቢን ሰይፍ አል-ታኒ አማካኝነት ነው። መልዕክተኛዋ በመግለጫቸው፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ የተመሰረተው የተመድ ቻርተር የህግ ሰነድ ብቻ ሳይሆን የጦርነትን አደጋ ለመከላከል ቃል የተገባበት የሞራል ስምምነት መሆኑን አስምረውበታል።
አክለውም አሁን ያለው በቻርተር ላይ የተመሰረተው ዓለም አቀፍ ስርዓት፣ የሀገራትን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በሚጥሱ አደገኛ ጥቃቶች ምክንያት ከዚህ ቀደም ታይቶ ለማይታወቅ ፈተና መጋለጡን ጠቁመዋል። እነዚህ ጥቃቶች የተመድን ተዓማኒነት የሚሸረሽሩ በመሆናቸው፣ ለቻርተሩ ቁርጠኛ የሆነ እና በተባበሩት መንግስታት በኩል ብዝሃነትን የሚያጠናክር እውነተኛ የፖለቲካ ፍላጎት ማምጣት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። አሁን ያሉትን ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎች ለመፍታት ከቻርተሩ አላማዎች እና ከተመድ ምስረታ ግቦች ጋር የሚጣጣም የጋራ ዓለም አቀፋዊ ምላሽ እንደሚያስፈልግም መልዕክተኛዋ አብራርተዋል።
በዚህ ረገድ ሼክ አሊያ የቻርተሩን መርሆዎች ሙሉ በሙሉ መተግበር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው፣ የቻርተሩን ድንጋጌዎች በሚተረጉሙበት ወቅት አድልዎ ከማድረግ መቆጠብ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም በሀገራት መካከል ያለውን የሉዓላዊነት እኩልነት መርህ በማጉላት፣ በተለይም አሁን ባለው የዓለም አቀፍ ህግ እና የዓለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ ግልጽ ጥሰቶች መሃል የኃይል እርምጃ መውሰድ ወይም በኃይል መዛት ሊከለከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የነባሩ ዓለም አቀፍ ስርዓት ዋነኛ ማዕቀፍ ሆኖ መቀጠሉ ወሳኝ መሆኑን ኳታር እንደምትገነዘብ ያነሱት መልዕክተኛዋ፣ ስርዓቱ የሃያ አንደኛውን ክፍለ ዘመን ተግዳሮቶች መቋቋም የሚችል፣ ሁሉን አቀፍ እና ውጤታማ እንዲሆን የተመድ ተቋማዊ ማሻሻያ በፍጥነት ሊተገበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ተቋሙ ተልዕኮውን በሚገባ እንዲወጣ በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል እና በተቋማዊ አቅም ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ግጭትን የመከላከል ስርዓት ላይ ኢንቨስት ማድረግ እና የግጭቶችን መንስኤዎች መፍታት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት መልዕክተኛዋ፣ ኳታር ሽምግልናን እና የመከላከያ ዲፕሎማሲን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ዋነኛ ምሰሶ አድርጋ እንደምትጠቀም አስታውሰዋል። ኳታር የተኩስ አቁም ስምምነቶችን፣ የፖለቲካ እስረኞች ልውውጥን፣ የግጭት አፈታት እና የሰላም ስምምነቶችን በተለያዩ አህጉራት በማመቻቸት የተመድ ስትራቴጂካዊ አጋር እና ታማኝ ዓለም አቀፍ አደራዳሪ መሆኗን አስመስክራለች ብለዋል።
የኳታር መንግስት በአሜሪካ እና በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መካከል ፓኪስታን እየመራች ላለው የሽምግልና ጥረት ምስጋናዋን እንደምታቀርብ እና ጥረቱንም እንደምትደግፍ አረጋግጠዋል። በቀጠናው ውጥረትን ለማርገብ፣ ሰላም እና መረጋጋትን ለማምጣት የሚያስችሉ እነዚህን የሽምግልና ጥረቶች ኳታር ሙሉ በሙሉ እንደምትደግፍም መልዕክተኛዋ አረጋግጠዋል።
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (ዩኤኢ) በሚገኘው የባራካህ የኒውክሌር ማብላያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት አጥብቆ አውግዟል።
ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ለጥቃቱ ማንንም አካል በግልጽ ተጠያቂ ከማድረግ ተቆጥቧል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀችው፣ ከኢራቅ ግዛት የተነሱ ስድስት የድሮን ጥቃቶች የተሰነዘሩባት ሲሆን፣ ከእነዚህም አንዱ በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ላይ የእሳት አደጋ አስከትሏል።
ኢራቅ በኢራን የሚደገፉ ጠንካራ ታጣቂ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱባት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። እነዚህ ታጣቂ ቡድኖች አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ባካሄዱት ጦርነት ወቅት፣ "በኢራቅ እና በቀጠናው በሚገኙ የጠላት የጦር ሰፈሮች" ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ኃላፊነት ሲወስዱ ቆይተዋል ሲል ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ለጥቃቱ ማንንም አካል በግልጽ ተጠያቂ ከማድረግ ተቆጥቧል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀችው፣ ከኢራቅ ግዛት የተነሱ ስድስት የድሮን ጥቃቶች የተሰነዘሩባት ሲሆን፣ ከእነዚህም አንዱ በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ላይ የእሳት አደጋ አስከትሏል።
ኢራቅ በኢራን የሚደገፉ ጠንካራ ታጣቂ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱባት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። እነዚህ ታጣቂ ቡድኖች አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ባካሄዱት ጦርነት ወቅት፣ "በኢራቅ እና በቀጠናው በሚገኙ የጠላት የጦር ሰፈሮች" ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ኃላፊነት ሲወስዱ ቆይተዋል ሲል ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን የጦር ኃይሎች ከፍተኛ ቃል አቀባይ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በሀገሪቱ ላይ የሚያካሂዱትን የአየር ድብደባ ዳግም የሚጀምሩ ከሆነ፣ ኢራን "እጅግ የከፋ" እና "በጣም ጠንካራ" የሆነ የአጸፋ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቀዋል።
አቦልፋዝል ሸካርቺ የተባሉት የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ በከፊል የመንግስት የዜና ወኪል በሆነው ፋርስ (Fars) በኩል በሰጡት መግለጫ፣ "ቀጠናው ወደ ሌላ ዙር ጦርነት የሚገባ ከሆነ፣ የኢራን ምላሽ ከቀጠናው ድንበሮችም የተሻገረ፣ እንዲሁም እጅግ የከፋ እና በጣም ጠንካራ ይሆናል" በማለት የሀገሪቱን አቋም አብራርተዋል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ይኸው የዜና ወኪል ባወጣው ዘገባ፣ የአሜሪካ እና የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች በሆርሙዝ ስትሬት (Strait of Hormuz) አቅራቢያ ከምትገኘው የላራክ ደሴት (Larak Island) በስተደቡብ በሚንቀሳቀሱ የኢራን ጀልባዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን እና በዚህም "በርካታ የኢራን ዜጎች" ህይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቆ ነበር።
እነዚህ የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች የተሰነዘሩት፣ በየካቲት ወር መጨረሻ አካባቢ በአሜሪካ እና በእስራኤል አነሳሽነት በኢራን ላይ የተከፈተውን እና ተከታትሎም የኢራንን የአጸፋ እርምጃ ያስተናገደውን ጦርነት በዘላቂነት ለማስቆም፣ በፓኪስታን አደራዳሪነት የሰላም ጥረቶች እየተካሄዱ ባሉበት ወቅት መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጨምሮታል።
አቦልፋዝል ሸካርቺ የተባሉት የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ በከፊል የመንግስት የዜና ወኪል በሆነው ፋርስ (Fars) በኩል በሰጡት መግለጫ፣ "ቀጠናው ወደ ሌላ ዙር ጦርነት የሚገባ ከሆነ፣ የኢራን ምላሽ ከቀጠናው ድንበሮችም የተሻገረ፣ እንዲሁም እጅግ የከፋ እና በጣም ጠንካራ ይሆናል" በማለት የሀገሪቱን አቋም አብራርተዋል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ይኸው የዜና ወኪል ባወጣው ዘገባ፣ የአሜሪካ እና የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች በሆርሙዝ ስትሬት (Strait of Hormuz) አቅራቢያ ከምትገኘው የላራክ ደሴት (Larak Island) በስተደቡብ በሚንቀሳቀሱ የኢራን ጀልባዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን እና በዚህም "በርካታ የኢራን ዜጎች" ህይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቆ ነበር።
እነዚህ የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች የተሰነዘሩት፣ በየካቲት ወር መጨረሻ አካባቢ በአሜሪካ እና በእስራኤል አነሳሽነት በኢራን ላይ የተከፈተውን እና ተከታትሎም የኢራንን የአጸፋ እርምጃ ያስተናገደውን ጦርነት በዘላቂነት ለማስቆም፣ በፓኪስታን አደራዳሪነት የሰላም ጥረቶች እየተካሄዱ ባሉበት ወቅት መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጨምሮታል።
9 days ago
ኢራን፣ አሜሪካ የፈጸመችው አዲስ ጥቃት የተኩስ አቁሙን የጣሰ ነው አለች
አሜሪካ ራስን መከላከል በሚል አዲስ ጥቃት በደቡባዊ ኢራን ከፈጸመች በኋላ ቴህራን ዋሺንግተን የተኩስ አቁሙን ጥሳለች ስትል ከሰሰች።
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በበኩላቸው በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረገውን ጦርነት ለማስቆም የሚደረገው ድርድር “ጥቂት ቀናት ሊወስድ ይችላል” ብለዋል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሜሪካ በደቡባዊ ኢራን ሆርሞዝጋን አውራጃ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቆ የተኩስ አቁሙ “ግልጽ ጥሰት ነው” ሲል ተናግሯል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አሜሪካ “ጠብ አጫሪ እና ተቀባይነት ለሌለው ድርጊቷ” ተጠያቂ ትሆናለች ብሏል።
አሜሪካ ጥቃት የፈጸመችበት ሆርሞዝጋን ክልል ከሆርሙዝ ወሽመጥ ጋር የሚዋሰን ነው።
ኢራን በመግለጫው “ያለምንም ጥርጥር የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ምላሽ ሳይሰጥ የሚተወው ምንም ክፋት የለም እንዲሁም የኢራን ዜጎችን ከመከላከልም ወደ ኋላ አይልም” ብላለች።
ሁለቱ አገራት እስከ ትናንት ሰኞ ድረስ በመግባቢያ ሰነዱ ዙሪያ የሚደረገው ንግግር ለውጥ ማሳየቱን ሲናገሩ ነበር።
አሜሪካ እና ኢራን የሚያደርጉት ንግግር በስምምነት ከተቋጨ ለሦስት ወር የዘለቀውን ጦርነቱን ያስቆማል፣ የሆርሙዝ ወሽመጥን ያስከፍታል እንዲሁም የተኩስ አቁሙን በ60 ቀናት ይራዘማል ተብሎ ነበር።
የአሜሪካ ጦር በደቡብ ኢራን የሚገኙ የሚሳዔል ማከማቻዎች እና ፈንጂ የሚጥሉ ጀልባዎችን ዒላማ በማድረግ አዲስ ዙር ጥቃት መክፈቱን አስታወቋል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ “ራስን መከላከል” እንደሆነ አስታውቋል።
ዓላማውም “በኢራን ኃይሎች ስጋት የተጋረጠባቸው ወታደሮቻችንን መከላከል ነው” ብሏል።
BBC
አሜሪካ ራስን መከላከል በሚል አዲስ ጥቃት በደቡባዊ ኢራን ከፈጸመች በኋላ ቴህራን ዋሺንግተን የተኩስ አቁሙን ጥሳለች ስትል ከሰሰች።
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በበኩላቸው በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረገውን ጦርነት ለማስቆም የሚደረገው ድርድር “ጥቂት ቀናት ሊወስድ ይችላል” ብለዋል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሜሪካ በደቡባዊ ኢራን ሆርሞዝጋን አውራጃ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቆ የተኩስ አቁሙ “ግልጽ ጥሰት ነው” ሲል ተናግሯል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አሜሪካ “ጠብ አጫሪ እና ተቀባይነት ለሌለው ድርጊቷ” ተጠያቂ ትሆናለች ብሏል።
አሜሪካ ጥቃት የፈጸመችበት ሆርሞዝጋን ክልል ከሆርሙዝ ወሽመጥ ጋር የሚዋሰን ነው።
ኢራን በመግለጫው “ያለምንም ጥርጥር የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ምላሽ ሳይሰጥ የሚተወው ምንም ክፋት የለም እንዲሁም የኢራን ዜጎችን ከመከላከልም ወደ ኋላ አይልም” ብላለች።
ሁለቱ አገራት እስከ ትናንት ሰኞ ድረስ በመግባቢያ ሰነዱ ዙሪያ የሚደረገው ንግግር ለውጥ ማሳየቱን ሲናገሩ ነበር።
አሜሪካ እና ኢራን የሚያደርጉት ንግግር በስምምነት ከተቋጨ ለሦስት ወር የዘለቀውን ጦርነቱን ያስቆማል፣ የሆርሙዝ ወሽመጥን ያስከፍታል እንዲሁም የተኩስ አቁሙን በ60 ቀናት ይራዘማል ተብሎ ነበር።
የአሜሪካ ጦር በደቡብ ኢራን የሚገኙ የሚሳዔል ማከማቻዎች እና ፈንጂ የሚጥሉ ጀልባዎችን ዒላማ በማድረግ አዲስ ዙር ጥቃት መክፈቱን አስታወቋል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ “ራስን መከላከል” እንደሆነ አስታውቋል።
ዓላማውም “በኢራን ኃይሎች ስጋት የተጋረጠባቸው ወታደሮቻችንን መከላከል ነው” ብሏል።
BBC
9 days ago
አሜሪካ የኢራን ሚሳዔል ማስወንጨፊያ ጣቢያን ደበደበች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ በማዕድን ማውጫ ጣቢያ ላይ የነበሩ ጀልባዎች ኢላማ መደረጋቸውን ገልጿል።
ዕዙ ጥቃት የፈጸመበትን ምክንያት ሲያስረዳ "ራስን ለመከላከል የተወሰደ እርምጃ" ነው ብሎታል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የመጨረሻውን ስምምነት ለማድረግ ከጫፍ ደርሰዋል እየተባለ ባለበት ወቅት ነው። #telegraph
Seledadotio
Seledadotio
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ በማዕድን ማውጫ ጣቢያ ላይ የነበሩ ጀልባዎች ኢላማ መደረጋቸውን ገልጿል።
ዕዙ ጥቃት የፈጸመበትን ምክንያት ሲያስረዳ "ራስን ለመከላከል የተወሰደ እርምጃ" ነው ብሎታል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የመጨረሻውን ስምምነት ለማድረግ ከጫፍ ደርሰዋል እየተባለ ባለበት ወቅት ነው። #telegraph
Seledadotio
Seledadotio
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን እና አካባቢው ያሉትን አጠቃላይ የአሜሪካ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የሚያስተባብረው ማዕከላዊ እዝ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ባወጣው መግለጫ፣ እነዚህ ክስተቶች ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የተፈጸሙ መሆናቸውን እና እርምጃው የአሜሪካ ጦርን ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተወሰደ መሆኑን አስታውቋል።
አሜሪካ በጦሯ ላይ በቀጥታ ጥቃት ተሰንዝሯል እያለች አይደለም። ይልቁንም በተለይ በሚሳኤል ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች እና ፈንጂዎችን ሊያጠምዱ በነበሩ ጀልባዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ በአካባቢው የሚገኙ ወታደሮቿን ለመጠበቅ የተደረገ 'የቅድመ መከላከል' እርምጃ መሆኑን ነው የገለጸችው።
እንዲህ ዓይነት ድርጊቶች ከዚህ ቀደምም ተከስተው ያውቃሉ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ በተጀመረበት የመጀመሪያ ጊዜ ተመሳሳይ ክስተት አጋጥሞ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ አሜሪካ ምንም ዓይነት የሰው ህይወት ጥፋት ባለመኖሩ ድርጊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደመጣስ እንደማይቆጠር ገልጻ ነበር።
አሁንም በተመሳሳይ በዚህኛው ክስተት፣ ምንም ዓይነት የአሜሪካ ጦር አባል እንዳልተገደለ ወይም እንዳልቆሰለ አሜሪካ አረጋግጣለች። ይህም ሁኔታው የተኩስ አቁም ስምምነቱን ወደ መጣስ ደረጃ እንደማይደርስ የሚያመላክት ነው። በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በርካታ ሀገራትን አሳትፎ እየተካሄደ ያለውን የድርድር ሂደት የሚያስተጓጉል አይሆንም።
ይሁን እንጂ፣ክስተቱ ለሁለቱም ሀገራት አሳሳቢ ወቅት መሆኑ አይካድም። ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ እርምጃ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል አሁንም ቢሆን ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ እንዳልለቀቀ የሚያስታውስ ነው።
አሜሪካ በጦሯ ላይ በቀጥታ ጥቃት ተሰንዝሯል እያለች አይደለም። ይልቁንም በተለይ በሚሳኤል ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች እና ፈንጂዎችን ሊያጠምዱ በነበሩ ጀልባዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ በአካባቢው የሚገኙ ወታደሮቿን ለመጠበቅ የተደረገ 'የቅድመ መከላከል' እርምጃ መሆኑን ነው የገለጸችው።
እንዲህ ዓይነት ድርጊቶች ከዚህ ቀደምም ተከስተው ያውቃሉ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ በተጀመረበት የመጀመሪያ ጊዜ ተመሳሳይ ክስተት አጋጥሞ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ አሜሪካ ምንም ዓይነት የሰው ህይወት ጥፋት ባለመኖሩ ድርጊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደመጣስ እንደማይቆጠር ገልጻ ነበር።
አሁንም በተመሳሳይ በዚህኛው ክስተት፣ ምንም ዓይነት የአሜሪካ ጦር አባል እንዳልተገደለ ወይም እንዳልቆሰለ አሜሪካ አረጋግጣለች። ይህም ሁኔታው የተኩስ አቁም ስምምነቱን ወደ መጣስ ደረጃ እንደማይደርስ የሚያመላክት ነው። በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በርካታ ሀገራትን አሳትፎ እየተካሄደ ያለውን የድርድር ሂደት የሚያስተጓጉል አይሆንም።
ይሁን እንጂ፣ክስተቱ ለሁለቱም ሀገራት አሳሳቢ ወቅት መሆኑ አይካድም። ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ እርምጃ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል አሁንም ቢሆን ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ እንዳልለቀቀ የሚያስታውስ ነው።