4 months ago
አማን ፍስሐፂዮን በአብሮ አደጎች ዕይታ
( ከዕዝራ እጅጉ)
#አማን በዳንኤል አሰፋ ዕይታ
#ethiopia | እኔ አማንን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በSandford English School አውቀዋለሁ። በዚያን ጊዜ ቅርብ ጓደኞች ነበርን፤ “Fantastic 5” ተብሎ የሚጠራ የልጅነት ቡድን ነበረን፣ እናም ቃሉን በብር ቀለም በእጆቻችን ላይ በኩራት እንፅፍ ነበር። እርሱ ቀድሞ ወደ አሜሪካ ሄደ፣ ነገር ግን ከሃይስኩል በኋላ በፔንሲልቬኒያ እንደገና ተገናኘን።
ኮሌጅ ሳለ ክብደት ያነሳ ስለነበር በጣም ጡንቻማ ሆኖ ያገኘሁትን ጊዜ አልረሳውም።
እርሱና ወንድሞቹ የኬብል ሥራ ንግድ ጀምረው ነበረ። ይህም ጥሩ ሁኖላቸው ነበር።። ነገር ግን ልቡ ሁልጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደሚፈልግ ይነግረኝ ነበር።
በእርግጥም ያንን አደረገ፤ ተመልሶም EBS የቲቪ ጣቢያን ጀመረ። ሁሉንም ችግሮች ተጋፍጦ ኢቢኤስ ለቁምነገር አበቃው። ሲያጋጥመው የነበረውን ጽናቱን እጅግ አደንቃለሁ።
ለእኔ ደስ የሚል ነገር ሁልጊዜ ከወደቀ በኃላ ዳግመኛ ተነስቶ ከቀድሞው ይልቅ ይበልጥ ስኬታማ መሆኑ ነበር።
በህመሙ ጊዜ ጥቂት ጊዜያት ጎበኘሁት፤ ሁልጊዜ አዎንታዊ፣ ተስፋ ያለው እና ጽኑ ፍላጎት ያለው ነበር — እውነተኛ ድንቅ ሰው! መጨረሻ ያየሁት በአዲስ አበባ በተካሄደው “Celebration of Life” ፓርቲው ላይ ነበር።
መጨረሻ በስልክ ያነጋገርኩት በጥቅምት ወር ነበር፣ በታኅሣሥም ልናገኘው ተዘጋጅተን ነበር፤ ነገር ግን ሞት ቀደመው።
#አማን በሔኖክ አስመሮም ዕይታ
እኔ ሁልጊዜ የአማንን ፈገግታና የልቡን ቸርነት አስታውሰዋለሁ። እርሱ ቁርጠኛና ትልቅ ራዕይ ያለው ሰው ነበር፤ በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ደስ ለማሰኘት የተፈጠረ የልዩ ስጦታ ባለቤት ነበር።
ትውውቃችን በሳንፎርድ ከስድስተኛ ክፍል ጀመረ። እስካሁንም ያ ትዝታ በአእምሮዬ አለ። ወደ ፓርቲ ለመሄድ ወይም በቦሌ ሚኒ በርገር ለመብላት እንድንሄድ የቤተሰቡን ፒክአፕ መኪና ከቤቱ በጸጥታ እየገፋን ስንወጣ የነበረውን ሳስብ እስቃለሁ። አማን ደፋርና እና እጅግ ታማኝ ነበር።
ለአገሩ ያለው ፍቅር የማይካድ ነበር፤ በፔን ስቴት በርቀት ሲኖርም ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በሐሳቡ ውስጥ ነበረች። ወደ አገሩ ለመመለስ በጣም ይመኝ ነበር—እናም ተመለሰ።
አማን ታላቅ ሰው፣ እውነተኛ ጓደኛና ወንድም ነበር። እጅግ ይናፍቃል። ነፍሱን ይማር!!!!
#አማንም በሰፈር አብሮ አደጎቹም የተወደደ ነበር
ፋሲል አለማየሁ ከአማን በ4 አመት ቢያንስም እነ አማን ቤት እየሄደ እንደ እኩያ ጓደኛ ይጫወት እንደነበር ያስታውሳል። አማን ታናናሾቹን በመንከባከብ እና ደስ ብሏቸው እንዲጫወቱ በማድረግ ትልቅ ሚና ነበረው። " በጣም የምወደው ልጅ ነበር። በጣም የሚያማምሩ ኮርስ ሳይክሎች ነበሩት። ቤታቸው 1,000 ካሬ ሜትርና ባለ አራት መኝታ ቤት ነው። ግቢው ሙሉ አስፋልት ሲሆን ለእኛ ለመጫወት ምቹም ነበር። ታዲያ አማን በጊዜው በዲኤክስ መኪና ይዞን ያንሸራሽረን እንደነበር ትዝ ይለኛል።" በማለት ፋሲል ትዝታውን አውግቶናል።
ፋሲል የልጅነት አብሮ አደጉ አማን ያደረገለትን ውለታ እንዲህ በማለት ያስታውሳል፦" አንድ ጊዜ የአባቴን መኪና በልጅነቴ ሰፈር ውስጥ ስነዳ ድንገት መኪናዋ ከፊት አካባቢ ተጋጨች። ይህን የሰማው አማን አባቴ ሳይሰማ መኪናውን ጋራዥ ወስዶ ከአባቴ ቁጣ እንድድን አድርጎኛል።" በማለት የአማንን ለችግር ደራሽነት ነግሮናል ።
አሁን ላሊበላ ሆቴል ያለበት ጋር ከእነ አማን ጋር ኳስ ይጫወት እንደነበር ፋሲል ያስታውሳል። አማን በ1980 ግድም የሀይስኩል ተማሪ ሳለ ወደ አሜሪካ ማቅናቱን ፋሲል ይናገራል። አማን ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ከአሜሪካ ሲመጣ ከፋሲል ጋር ተገናኝተው ነበር። ፋሲል በአማን እረፍት ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ነግሮናል። "ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳላየው ፣ ነገ ዛሬ አገኘዋለሁ እያልኹ በማረፉ አዝኛለሁ " ብሎናል።
#ቀፀላወርቅ ሰይፉ ስለ አማን
ቀፀላወርቅ ሰይፉ የአንጋፋዋ ጋዜጠኛ የወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ልጅ ስትሆን የተማረችው ሳንፎርድ ነው። አማንን በትንሽ ክፍል ብትበልጠውም ( ሲኒየሩ ብትሆንም- እርሱ ግን ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳንፎርድ ተምረናል ብሎ አስታውሶ ሰላምታ እንዳቀረበላት ታስታውሳለች።
ቀፀላወርቅ ሰይፉ አማን ከቅርቦቹ ጋር ሆኖ ኢቢኤስን የጀመረ ሰሞን አግኝታው እንደነበር ትናገራለች። በአፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አየር ላይ ለማዋሀል አጭር የተነደፈ ዕቅድ አዘጋጂ ብሏት እንደነበር ትዝ ይላታል። ቀፀላ በራሷ ምክንያት የዛን ጊዜውን እቅድ ተግባራዊ ባታደርገውም የዛሬ አመት 2017 ግድም ድጋሚ ሥራውን ለመጀመር ከአማን ጋር ጭውውት አድርጋ ነበር።
"...ከአማን ጋር በፕሮግራሙ ዙሪያ ከ 2 ሰዓት በላይ ተነጋግረናል። በሚድያ ላይ ያለው እውቀት ምን ያህል የዳበረ እንደሆነ ግንዛቤ አግኝቻለሁ።የህመም ስሜት እንዳለው ያጫውተኝ ነበር። በዕውነቱ የአማን ህልፈት ለኢትዮጵያ ትልቅ እጦት ነው" በማለት ቀፀላ ምስክርነት ሰጥታለች ።
#ዮናስ ማህረነ ስለ አማን
ዮናስ ማህረነ ከአማን ጋር ሳንፎርድ ከተማሩ ጓደኞቹ አንዱ ነው። ምስክርቱን እንደሚከተለው ሰጥቶናል፦
"........አማን ጨዋታ የሚችል እና ደግ ነበር። ኳስ እንጫወት ነበር። እኔ በረኛ ነበርኩ። አማን መሀል ነው። 1992 በፈረንጆች አቆጣጠር ላይ ከብዙ ጊዜ በኃላ አገኘሁት። 'ሞንክ 'ብሎ በትምህርት ቤት የቅፅል ስሜ ጮሆ ጠራኝ። በጊዜው ክብደት ያነሳ ስለነበር ወፍሮ ጠበቀኝ። 2004 እ.ኤ.አ አሜሪካ አብረን የተማርን አብሮ አደጎቹ ቤቱ ሄደን ጠየቅነው። አማን ከእኛ ቡድን የሚለየው ቢዝነስ ላይ ጥሩ ነበር። የሥራ የመፍጠር ክህሎት ነበረው።አሜሪካ ሳለ calling card ቢዝነስ ነበረው። የማስደወል ቢዝነስ ይሠራ ነበር። ወንድማችን አማን ከድሮም ደግነትን የተላበሰ ወንድማችን ነበር። መሞቱን ግሩም ነው የነገረኝ። ህዳር ላይ ሆስፒታል ሄደን ልንጠይቀው ነበር። ነገር ግን ማለፉ ሲሰማ ጥልቅ ሀዘን ነው የተሰማኝ።" በማለት ዮናስ ማህረነ ከአሜሪካ ሆኖ ምስክርነት ሰጥቷል።
የእነ አማን ሰፈር
አማን ከአንደኛ ክፍል እስከ 7ኛ ማለትም ከ1970-1977 የተማረው ሳንፎርድ ትምህርት ቤት ሲሆን ለቤቱም የመጨረሻ ልጅ ነው። ከ8ኛ ክፍል በኃላ የሁለተኛ ደረጃ እና የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን በአሜሪካን አገር ነበር የተከታተለው።የዛን ጊዜ ቤታቸው ቀበሌ 20 አሁን ስካይላይት ጀርባ የቻይና ኤምባሲ ያለበት የእነ አማን ቤት ነበር። የአማን አባት አቶ ፍስሐፂዮን ገብረህይወት 'ባድራግ' የተሰኘ ጎማ አስመጪ ነበሩ። ደርግም ለተወሰኑ ዓመታት ለእስር ዳርጓቸው ነበር። የቤቱ የመጨረሻ ልጅ አማን ሰፈር ኳስ በመጫወት ያሳልፍ እንደነበር አብረውት ያደጉ ልጆችን በማነጋገር ማረጋገጥ ችለናል።
#አማን በሳንፎርድ
በአንድ ክፍል ውስጥ 20 ልጆች ብቻ የሚማሩበት ሳንፎርድ በዚያን ጊዜ በዓመት 4,000 ብር ለአንድ ልጅ የሚከፈልበት ተማሪ ቤት ሲሆን የትምህርት ሥርዓቱም ዓለምአቀፍ ደረጃ በመሆኑ ተማሪዎች በጥራት እንዲማሩ ይደረጋል። ግሩም ፋንቱ ሳንፎርድ ከአማን ጋር አብሮ ተምሯል።ግሩም ለዚህ የሕይወት ታሪክ አዘጋጅ እንዳጫወተው አማን ከልጅነት ጀምሮ ቀናነት የተላበሰ እና በወጉ በጥሩ ሁኔታ ያደገ ልጅ ባህሪይ ያሳይ እንደነበር ተናግሯል።
"...አማን ጋር ኤለመንተሪ ስንማር ይህን ቀናነቱን እና ከሰው ጋር ያለውን ተግባቢነት አስተውል ነበር። በኃላ ካደግን በኃላ ኒዮርክ ፊላደልፊያ አግኝቼው የድሮ ተግባቢነቱ ሳይቀየር አነኘሁ" ብሎናል።
"አማን ሳንፎርድ ሳለን የቅርጫት ኳስም ይጫወት ነበር። ተግባቢነቱ እዚህም ላይ ነበር። አብረውን ከተማሩት መካከል የእኛ ሁለት ዓመት ሲኒየር ብትሆንም ቀፀላወርቅ ሰይፉ፣ ያሲር ባገርሽ የሚጠቀሱ ናቸው። ያኔ አብረን ጓደኛሞች የነበርነው እኔ( ግሩም ፋንቱ)፣ ሔኖክ አስመሮም፣ኢክረም ሰኢድ፣ ዳንኤል አሰፋ፣ዮሐንስ ማህረነ፣ነበርን።ኢክረም ሰኢድ (አርፏል) እና አማን በሁላችንም የሚወደድ ልጅ ነበር። አለባበሱም ምርጥ ነበር። ካደገም በኃላ አለባበስ ላይ ጥሩ ነው። አማን የቤቱ መጨረሻ ሲሆን እህት ወንድሞቹ ቀድመው ነበር ውጭ የሄዱት። "በማለት ግሩም ምስክርነቱን ሰጥቶናል።
#ከአማን ጋር ሳንፎርድ አብራ የተማረችው ሀናን አብደላ ስለ አማን ስትናገር ገና 4ኛ ክፍል ሳለ ያለውን የአእምሮ ብስለት ወይሞ imotional intelligence ታደንቃለች። በልጅነቱ አማን ምንም ነገር ቢያጋጥመው ስሜት የመቆጣጠር ችሎታው ትልቅ እንደነበር አስታውሳለሁ ስትልም ወደ ኃላ መለስ ብላ ታስታውሳለች።
"....አማን በጣም የምናከብረው ወንድማችን ነው። ከብዙ ጊዜ በኃላ ሲያገኘኝ ሀናን ረሳሽኝ እንዴ ብሎ እንደ ልጅነታችን ሰላምታ የሚሰጠኝ አብሮ አደጌ ነው። አንዳንድ ሰው አብረኸው ተምረህ እያየህ ዝም ሊልህ ይችላል አማን ግን እንደዚያ አይደለም። እሱን በማጣታችን እጅግ አዝነናል።" በማለት ሀናን ምስክርነት ሰጥታለች።
( ከዕዝራ እጅጉ)
#አማን በዳንኤል አሰፋ ዕይታ
#ethiopia | እኔ አማንን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በSandford English School አውቀዋለሁ። በዚያን ጊዜ ቅርብ ጓደኞች ነበርን፤ “Fantastic 5” ተብሎ የሚጠራ የልጅነት ቡድን ነበረን፣ እናም ቃሉን በብር ቀለም በእጆቻችን ላይ በኩራት እንፅፍ ነበር። እርሱ ቀድሞ ወደ አሜሪካ ሄደ፣ ነገር ግን ከሃይስኩል በኋላ በፔንሲልቬኒያ እንደገና ተገናኘን።
ኮሌጅ ሳለ ክብደት ያነሳ ስለነበር በጣም ጡንቻማ ሆኖ ያገኘሁትን ጊዜ አልረሳውም።
እርሱና ወንድሞቹ የኬብል ሥራ ንግድ ጀምረው ነበረ። ይህም ጥሩ ሁኖላቸው ነበር።። ነገር ግን ልቡ ሁልጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደሚፈልግ ይነግረኝ ነበር።
በእርግጥም ያንን አደረገ፤ ተመልሶም EBS የቲቪ ጣቢያን ጀመረ። ሁሉንም ችግሮች ተጋፍጦ ኢቢኤስ ለቁምነገር አበቃው። ሲያጋጥመው የነበረውን ጽናቱን እጅግ አደንቃለሁ።
ለእኔ ደስ የሚል ነገር ሁልጊዜ ከወደቀ በኃላ ዳግመኛ ተነስቶ ከቀድሞው ይልቅ ይበልጥ ስኬታማ መሆኑ ነበር።
በህመሙ ጊዜ ጥቂት ጊዜያት ጎበኘሁት፤ ሁልጊዜ አዎንታዊ፣ ተስፋ ያለው እና ጽኑ ፍላጎት ያለው ነበር — እውነተኛ ድንቅ ሰው! መጨረሻ ያየሁት በአዲስ አበባ በተካሄደው “Celebration of Life” ፓርቲው ላይ ነበር።
መጨረሻ በስልክ ያነጋገርኩት በጥቅምት ወር ነበር፣ በታኅሣሥም ልናገኘው ተዘጋጅተን ነበር፤ ነገር ግን ሞት ቀደመው።
#አማን በሔኖክ አስመሮም ዕይታ
እኔ ሁልጊዜ የአማንን ፈገግታና የልቡን ቸርነት አስታውሰዋለሁ። እርሱ ቁርጠኛና ትልቅ ራዕይ ያለው ሰው ነበር፤ በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ደስ ለማሰኘት የተፈጠረ የልዩ ስጦታ ባለቤት ነበር።
ትውውቃችን በሳንፎርድ ከስድስተኛ ክፍል ጀመረ። እስካሁንም ያ ትዝታ በአእምሮዬ አለ። ወደ ፓርቲ ለመሄድ ወይም በቦሌ ሚኒ በርገር ለመብላት እንድንሄድ የቤተሰቡን ፒክአፕ መኪና ከቤቱ በጸጥታ እየገፋን ስንወጣ የነበረውን ሳስብ እስቃለሁ። አማን ደፋርና እና እጅግ ታማኝ ነበር።
ለአገሩ ያለው ፍቅር የማይካድ ነበር፤ በፔን ስቴት በርቀት ሲኖርም ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በሐሳቡ ውስጥ ነበረች። ወደ አገሩ ለመመለስ በጣም ይመኝ ነበር—እናም ተመለሰ።
አማን ታላቅ ሰው፣ እውነተኛ ጓደኛና ወንድም ነበር። እጅግ ይናፍቃል። ነፍሱን ይማር!!!!
#አማንም በሰፈር አብሮ አደጎቹም የተወደደ ነበር
ፋሲል አለማየሁ ከአማን በ4 አመት ቢያንስም እነ አማን ቤት እየሄደ እንደ እኩያ ጓደኛ ይጫወት እንደነበር ያስታውሳል። አማን ታናናሾቹን በመንከባከብ እና ደስ ብሏቸው እንዲጫወቱ በማድረግ ትልቅ ሚና ነበረው። " በጣም የምወደው ልጅ ነበር። በጣም የሚያማምሩ ኮርስ ሳይክሎች ነበሩት። ቤታቸው 1,000 ካሬ ሜትርና ባለ አራት መኝታ ቤት ነው። ግቢው ሙሉ አስፋልት ሲሆን ለእኛ ለመጫወት ምቹም ነበር። ታዲያ አማን በጊዜው በዲኤክስ መኪና ይዞን ያንሸራሽረን እንደነበር ትዝ ይለኛል።" በማለት ፋሲል ትዝታውን አውግቶናል።
ፋሲል የልጅነት አብሮ አደጉ አማን ያደረገለትን ውለታ እንዲህ በማለት ያስታውሳል፦" አንድ ጊዜ የአባቴን መኪና በልጅነቴ ሰፈር ውስጥ ስነዳ ድንገት መኪናዋ ከፊት አካባቢ ተጋጨች። ይህን የሰማው አማን አባቴ ሳይሰማ መኪናውን ጋራዥ ወስዶ ከአባቴ ቁጣ እንድድን አድርጎኛል።" በማለት የአማንን ለችግር ደራሽነት ነግሮናል ።
አሁን ላሊበላ ሆቴል ያለበት ጋር ከእነ አማን ጋር ኳስ ይጫወት እንደነበር ፋሲል ያስታውሳል። አማን በ1980 ግድም የሀይስኩል ተማሪ ሳለ ወደ አሜሪካ ማቅናቱን ፋሲል ይናገራል። አማን ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ከአሜሪካ ሲመጣ ከፋሲል ጋር ተገናኝተው ነበር። ፋሲል በአማን እረፍት ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ነግሮናል። "ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳላየው ፣ ነገ ዛሬ አገኘዋለሁ እያልኹ በማረፉ አዝኛለሁ " ብሎናል።
#ቀፀላወርቅ ሰይፉ ስለ አማን
ቀፀላወርቅ ሰይፉ የአንጋፋዋ ጋዜጠኛ የወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ልጅ ስትሆን የተማረችው ሳንፎርድ ነው። አማንን በትንሽ ክፍል ብትበልጠውም ( ሲኒየሩ ብትሆንም- እርሱ ግን ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳንፎርድ ተምረናል ብሎ አስታውሶ ሰላምታ እንዳቀረበላት ታስታውሳለች።
ቀፀላወርቅ ሰይፉ አማን ከቅርቦቹ ጋር ሆኖ ኢቢኤስን የጀመረ ሰሞን አግኝታው እንደነበር ትናገራለች። በአፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አየር ላይ ለማዋሀል አጭር የተነደፈ ዕቅድ አዘጋጂ ብሏት እንደነበር ትዝ ይላታል። ቀፀላ በራሷ ምክንያት የዛን ጊዜውን እቅድ ተግባራዊ ባታደርገውም የዛሬ አመት 2017 ግድም ድጋሚ ሥራውን ለመጀመር ከአማን ጋር ጭውውት አድርጋ ነበር።
"...ከአማን ጋር በፕሮግራሙ ዙሪያ ከ 2 ሰዓት በላይ ተነጋግረናል። በሚድያ ላይ ያለው እውቀት ምን ያህል የዳበረ እንደሆነ ግንዛቤ አግኝቻለሁ።የህመም ስሜት እንዳለው ያጫውተኝ ነበር። በዕውነቱ የአማን ህልፈት ለኢትዮጵያ ትልቅ እጦት ነው" በማለት ቀፀላ ምስክርነት ሰጥታለች ።
#ዮናስ ማህረነ ስለ አማን
ዮናስ ማህረነ ከአማን ጋር ሳንፎርድ ከተማሩ ጓደኞቹ አንዱ ነው። ምስክርቱን እንደሚከተለው ሰጥቶናል፦
"........አማን ጨዋታ የሚችል እና ደግ ነበር። ኳስ እንጫወት ነበር። እኔ በረኛ ነበርኩ። አማን መሀል ነው። 1992 በፈረንጆች አቆጣጠር ላይ ከብዙ ጊዜ በኃላ አገኘሁት። 'ሞንክ 'ብሎ በትምህርት ቤት የቅፅል ስሜ ጮሆ ጠራኝ። በጊዜው ክብደት ያነሳ ስለነበር ወፍሮ ጠበቀኝ። 2004 እ.ኤ.አ አሜሪካ አብረን የተማርን አብሮ አደጎቹ ቤቱ ሄደን ጠየቅነው። አማን ከእኛ ቡድን የሚለየው ቢዝነስ ላይ ጥሩ ነበር። የሥራ የመፍጠር ክህሎት ነበረው።አሜሪካ ሳለ calling card ቢዝነስ ነበረው። የማስደወል ቢዝነስ ይሠራ ነበር። ወንድማችን አማን ከድሮም ደግነትን የተላበሰ ወንድማችን ነበር። መሞቱን ግሩም ነው የነገረኝ። ህዳር ላይ ሆስፒታል ሄደን ልንጠይቀው ነበር። ነገር ግን ማለፉ ሲሰማ ጥልቅ ሀዘን ነው የተሰማኝ።" በማለት ዮናስ ማህረነ ከአሜሪካ ሆኖ ምስክርነት ሰጥቷል።
የእነ አማን ሰፈር
አማን ከአንደኛ ክፍል እስከ 7ኛ ማለትም ከ1970-1977 የተማረው ሳንፎርድ ትምህርት ቤት ሲሆን ለቤቱም የመጨረሻ ልጅ ነው። ከ8ኛ ክፍል በኃላ የሁለተኛ ደረጃ እና የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን በአሜሪካን አገር ነበር የተከታተለው።የዛን ጊዜ ቤታቸው ቀበሌ 20 አሁን ስካይላይት ጀርባ የቻይና ኤምባሲ ያለበት የእነ አማን ቤት ነበር። የአማን አባት አቶ ፍስሐፂዮን ገብረህይወት 'ባድራግ' የተሰኘ ጎማ አስመጪ ነበሩ። ደርግም ለተወሰኑ ዓመታት ለእስር ዳርጓቸው ነበር። የቤቱ የመጨረሻ ልጅ አማን ሰፈር ኳስ በመጫወት ያሳልፍ እንደነበር አብረውት ያደጉ ልጆችን በማነጋገር ማረጋገጥ ችለናል።
#አማን በሳንፎርድ
በአንድ ክፍል ውስጥ 20 ልጆች ብቻ የሚማሩበት ሳንፎርድ በዚያን ጊዜ በዓመት 4,000 ብር ለአንድ ልጅ የሚከፈልበት ተማሪ ቤት ሲሆን የትምህርት ሥርዓቱም ዓለምአቀፍ ደረጃ በመሆኑ ተማሪዎች በጥራት እንዲማሩ ይደረጋል። ግሩም ፋንቱ ሳንፎርድ ከአማን ጋር አብሮ ተምሯል።ግሩም ለዚህ የሕይወት ታሪክ አዘጋጅ እንዳጫወተው አማን ከልጅነት ጀምሮ ቀናነት የተላበሰ እና በወጉ በጥሩ ሁኔታ ያደገ ልጅ ባህሪይ ያሳይ እንደነበር ተናግሯል።
"...አማን ጋር ኤለመንተሪ ስንማር ይህን ቀናነቱን እና ከሰው ጋር ያለውን ተግባቢነት አስተውል ነበር። በኃላ ካደግን በኃላ ኒዮርክ ፊላደልፊያ አግኝቼው የድሮ ተግባቢነቱ ሳይቀየር አነኘሁ" ብሎናል።
"አማን ሳንፎርድ ሳለን የቅርጫት ኳስም ይጫወት ነበር። ተግባቢነቱ እዚህም ላይ ነበር። አብረውን ከተማሩት መካከል የእኛ ሁለት ዓመት ሲኒየር ብትሆንም ቀፀላወርቅ ሰይፉ፣ ያሲር ባገርሽ የሚጠቀሱ ናቸው። ያኔ አብረን ጓደኛሞች የነበርነው እኔ( ግሩም ፋንቱ)፣ ሔኖክ አስመሮም፣ኢክረም ሰኢድ፣ ዳንኤል አሰፋ፣ዮሐንስ ማህረነ፣ነበርን።ኢክረም ሰኢድ (አርፏል) እና አማን በሁላችንም የሚወደድ ልጅ ነበር። አለባበሱም ምርጥ ነበር። ካደገም በኃላ አለባበስ ላይ ጥሩ ነው። አማን የቤቱ መጨረሻ ሲሆን እህት ወንድሞቹ ቀድመው ነበር ውጭ የሄዱት። "በማለት ግሩም ምስክርነቱን ሰጥቶናል።
#ከአማን ጋር ሳንፎርድ አብራ የተማረችው ሀናን አብደላ ስለ አማን ስትናገር ገና 4ኛ ክፍል ሳለ ያለውን የአእምሮ ብስለት ወይሞ imotional intelligence ታደንቃለች። በልጅነቱ አማን ምንም ነገር ቢያጋጥመው ስሜት የመቆጣጠር ችሎታው ትልቅ እንደነበር አስታውሳለሁ ስትልም ወደ ኃላ መለስ ብላ ታስታውሳለች።
"....አማን በጣም የምናከብረው ወንድማችን ነው። ከብዙ ጊዜ በኃላ ሲያገኘኝ ሀናን ረሳሽኝ እንዴ ብሎ እንደ ልጅነታችን ሰላምታ የሚሰጠኝ አብሮ አደጌ ነው። አንዳንድ ሰው አብረኸው ተምረህ እያየህ ዝም ሊልህ ይችላል አማን ግን እንደዚያ አይደለም። እሱን በማጣታችን እጅግ አዝነናል።" በማለት ሀናን ምስክርነት ሰጥታለች።