3 days ago
3 days ago
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው
#ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል #election #fanadigital #ethiopia #ethiopiavotes #democracy #fanatelevision
3 days ago
ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | ግንቦት 24፣ 2018 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል"
በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጋዜጣ-ፕላስ
#የ7ኛውጠቅላላምርጫ #ምርጫ2018 #ሻሻ #ጠቅላይሚኒስትርዐቢይ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ግንቦት 24፣ 2018 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል"
በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጋዜጣ-ፕላስ
#የ7ኛውጠቅላላምርጫ #ምርጫ2018 #ሻሻ #ጠቅላይሚኒስትርዐቢይ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
#ምርጫ2018
በምርጫው ድምፅ የተሰጠባቸውን ወረቀቶች ዋጋ አልባ የሚያደርጓችው ምክንያቶች የትኞቹ ናቸው ?
1. የመራጩ ማንነት በስም የተገለጸ ከሆነ፣
2. ለምክር ቤቱ ሊመረጥ ከሚቻለው ተመራጮች ቁጥር በላይ ላላቸው ዕጩዎች ምልክት የተደረገበት ከሆነ፣
3. ምንም ምልክት ያልተደረገበት ከሆነ፣
4. መራጩ ማንን አንደመረጠ መለየት የሚያስቸግር ከሆነ፣
5. ሕጋዊ የድምፅ መስጫ ወረቀት ያልሆነ ወይም በምርጫ ጣቢያው ያልተሠራጨ የድምፅ መስጫ ወረቀት ከሆነ ዋጋ አልባ ይሆናል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በምርጫው ድምፅ የተሰጠባቸውን ወረቀቶች ዋጋ አልባ የሚያደርጓችው ምክንያቶች የትኞቹ ናቸው ?
1. የመራጩ ማንነት በስም የተገለጸ ከሆነ፣
2. ለምክር ቤቱ ሊመረጥ ከሚቻለው ተመራጮች ቁጥር በላይ ላላቸው ዕጩዎች ምልክት የተደረገበት ከሆነ፣
3. ምንም ምልክት ያልተደረገበት ከሆነ፣
4. መራጩ ማንን አንደመረጠ መለየት የሚያስቸግር ከሆነ፣
5. ሕጋዊ የድምፅ መስጫ ወረቀት ያልሆነ ወይም በምርጫ ጣቢያው ያልተሠራጨ የድምፅ መስጫ ወረቀት ከሆነ ዋጋ አልባ ይሆናል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
#ምርጫ2018
ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ገዢው ብልፅግና ፓርቲም ለመጪው ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን እያስተዋወቀ ሲሆን ከነዚህም እጩዎች መካከል ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት ፣ እንዲሁም አርሶ አደር የሆኑ ይገኙበታል።
በአዲስ አበባ ለምክር ቤት እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አንደኛው በሙዚቃ አቀናባሪነት የሚታወቀው ካሙዙ ካሳ ነው።
ሙዚቀኛው ፥ ስራው አርቲስት ፣ የትምህርት ደረጃው መካከለኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም የሚወዳደረው የካ ክፍለ ከተማ መሆኑ ተገልጾ ይፋ ተደርጓል።
ሌላኛዋ የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ ወ/ሮ በሻቱ ቶሎማርያም እዛው የካ ክፍለ ከተማ እጩ ሆና ቀርባለች።
ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሹሜ ግዛው የተባሉ አርሶ አደርም በእጩነት ቀርበዋል።
በዚህ ክፍለ ከተማ ሌሎች በፌዴራል ደረጃ፣ በከተማ፣ በክፍለ ከተማ አመራርነት ላይ የሚገኙ እጩዎችም ቀርበዋል።
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡ እጩዎች መካከል ደግሞ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ ወ/ሮ አይሻ መሃመድ ፣ ዶ/ር ሌሊሴ ነሜ ይገኙበታል።
መረጃው የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ገዢው ብልፅግና ፓርቲም ለመጪው ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን እያስተዋወቀ ሲሆን ከነዚህም እጩዎች መካከል ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት ፣ እንዲሁም አርሶ አደር የሆኑ ይገኙበታል።
በአዲስ አበባ ለምክር ቤት እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አንደኛው በሙዚቃ አቀናባሪነት የሚታወቀው ካሙዙ ካሳ ነው።
ሙዚቀኛው ፥ ስራው አርቲስት ፣ የትምህርት ደረጃው መካከለኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም የሚወዳደረው የካ ክፍለ ከተማ መሆኑ ተገልጾ ይፋ ተደርጓል።
ሌላኛዋ የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ ወ/ሮ በሻቱ ቶሎማርያም እዛው የካ ክፍለ ከተማ እጩ ሆና ቀርባለች።
ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሹሜ ግዛው የተባሉ አርሶ አደርም በእጩነት ቀርበዋል።
በዚህ ክፍለ ከተማ ሌሎች በፌዴራል ደረጃ፣ በከተማ፣ በክፍለ ከተማ አመራርነት ላይ የሚገኙ እጩዎችም ቀርበዋል።
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡ እጩዎች መካከል ደግሞ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ ወ/ሮ አይሻ መሃመድ ፣ ዶ/ር ሌሊሴ ነሜ ይገኙበታል።
መረጃው የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
3 months ago
🗳️ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ9 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
3 months ago
ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከ10 ሺህ በላይ እጩዎች ለውድድር ቀረቡ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያጠናቀቀ መሆኑን ገለጸ። ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ፣ ለዘንድሮው ምርጫ በአጠቃላይ 10 ሺህ 934 እጩ ተወዳዳሪዎች መመዝገባቸውን ይፋ አድርጓል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንደገለጹት፣ የምዝገባ ሂደቱ በዲጂታል ስርዓት የተከናወነ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የቀረቡት በሁለት ዘርፍ ነው፦
* ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፦ 2 ሺህ 198 እጩዎች
* ለክልል ምክር ቤቶች፦ 8 ሺህ 736 እጩዎች
የተሳታፊዎች ስብጥር፦
* በድምሩ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፣
* በተጨማሪም 73 የግል እጩዎች ለውድድር መቅረባቸው ታውቋል።
ቦርዱ አክሎም፣ የእጩዎች ዝርዝር ነገ ይፋ እንደሚደረግና ከዜጎች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ይህም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #ዴሞክራሲ #ዜና #ethiopia #election2026
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያጠናቀቀ መሆኑን ገለጸ። ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ፣ ለዘንድሮው ምርጫ በአጠቃላይ 10 ሺህ 934 እጩ ተወዳዳሪዎች መመዝገባቸውን ይፋ አድርጓል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንደገለጹት፣ የምዝገባ ሂደቱ በዲጂታል ስርዓት የተከናወነ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የቀረቡት በሁለት ዘርፍ ነው፦
* ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፦ 2 ሺህ 198 እጩዎች
* ለክልል ምክር ቤቶች፦ 8 ሺህ 736 እጩዎች
የተሳታፊዎች ስብጥር፦
* በድምሩ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፣
* በተጨማሪም 73 የግል እጩዎች ለውድድር መቅረባቸው ታውቋል።
ቦርዱ አክሎም፣ የእጩዎች ዝርዝር ነገ ይፋ እንደሚደረግና ከዜጎች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ይህም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #ዴሞክራሲ #ዜና #ethiopia #election2026
Sponsored by
Surafel