Logo
Getu Temesgen
ጉግል በክሮም የመረጃ ማፈላለጊያ ላይ ለተከሰተዉ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት ማስተካከያ ለቀቀ
#ethiopia | ጉግል በክሮም የመረጃ ማፈላለጊያ #browser ላይ የታዩና ቀድሞ ያልተለዩ #zero_day ተጋላጭነቶችን የሚቀርፍ የደህንነት ማሻሻያዎችን ለቀቀ፡፡

ይህ ክፍተት (CVE-2025-10585) አደገኛ ከሚባሉ ክፍተቶች መካከል የሚመደብ እንደሆነ ጎግል ገልጿል፡፡ እንዲህ አይነት ቀድሞ ያልተለዩ (zero-day) ተጋላጭነቶች በፈረንጆቹ 2025 ብቻ በክሮም ላይ ለስድስተኛ ጊዜ እንደተከሰቱ ኩባንያው አስታውቋል፡፡

በመሆኑም ከዚህ አደጋ ስጋት ለመጠበቅ የጎግል ክሮም የመረጃ ማፈላልጊያ ከዚህ በታች በተዘረዘረው ስሪት መሰረት ማዘመን እንደሚያስፈልግ ጉግል አሳስቧል፡፡

ዊንዶውስ #windows እና ማክ ኦኤስ #macos ምርት ተጠቃሚዎች ወደ ክሮም ስሪት: 140.0.7339.185/.186 ማዘመን እንዲሁም የሊነክስ #linux ምርት ተጠቃሚዎች ደግሞ ወደ ክሮም ስሪት፡140.0.7339.185 ማዘመን ይጠበቅባቸዋል።
በተጨማሪም እንደ #microsoft_edge፣ #brave፣ #opera እና #vivaldi ያሉ ሌሎች በክሮሚየም #chromium ላይ ለተመሰረቱ የመረጃ ማፈላልጊያዎች ላይ የክፍተት መሙያ መለቀቁንና ተጠቃሚዎች በፍጥነት እንዲያዘመኑም ኩባንያው መክሯል።

እርስዎም ወደ ክሮም የመረጃ ማፈላልጊያ በመሄድ ክሮም ምርትዎን በማዘመን ሊደርስብዎት የሚችለዉን የጥቃት ተገላጭነት ይድፈኑ።#insa

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.