ለመላው የሕግ ባለሞያ ማህበረሰብ፡ አዲስ የሕግ ምሩቃን እና ተማሪዎች በሙሉ መልካም ዜና!
የሕግ አገልግሎትን የሚያዘምን እና ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ይፋ ሊሆን ነው!
የሕግ ቴክኖሎጂን(LegTech) በመጠቀም በኢትዮጵያ የጥብቅና አገልግሎትን ዘመናዊ ለማድረግ እና ተደራሽነትን ለማስፋት ያለመ ነው::
ኢትዮ ሌጋል ሺልድ ሀላፊነቱ የተወሰነ የጥብቅና ማህበር ከገበያ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ለብዙዎች የሥራ ዕድል የሚፈጥርና ባለሞያውን በቀላሉ ከአገልግሎት ፈላጊው ጋር የሚያገናኝ (AI-powered Legal talent cloud and Matching platform) በቴክኖሎጂ የታገዘ የህግ አገልግሎት ይዞላችሁ ቀርቧል።
ይህ አገልግሎት የህግ ባለሙያዎችንና ደንበኞችን በቀጥታ የሚያገናኝ ከመሆኑ ባሻገር የሕግ አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ የመክፈል አቅም እና የቦታ ርቀት ውስንነት ሳይገደብ ተደራሽ የሚያደርግ በመሆኑ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው።
ይህን ወሳኝ አዲስ ጅምር ለማስተዋወቅ በተዘጋጀው ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀ ግብራችን ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
በዝግጅቱ ላይ፡
• "በቴክኖሎጅ የታገዘ የህግ አገልግሎት በኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ፣ የህግ ቴክኖሎጂ ለፍትህ ተደራሽነትና ለዘርፉ እድገት ስላለው አስተዋጽኦ የሚመክር የፓናል ውይይት ይካሄዳል።
• ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሕግ ግንዛቤ ማስጨበጫ እና የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ለማገልገል የተዘጋጀውን ልዩ የህግ አገልግሎት ለተሳታፊዎች እናስተዋውቃለን።
• የህግ ባለሙያዎች፣ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች፣ የመንግስት ባለድርሻ አካላትና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዚህ ዝግጅት ላይ ተገኝተው ስለህግና ቴክኖሎጂ የወደፊት ሁኔታ ይወያያሉ።
የዝግጅቱ ዝርዝር
• 📅 : ማክሰኞ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
• 🕙: ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ቀኑ 6፡00
• 📍: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት፣ 5ኛ ፎቅ፣ አዲስ አበባ
ለመሳተፍ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ በመጫን ፤መረጃዎን የተሳታፊዎች ዝርዝር ወስጥ በማስመዝገብ ወደ ዝግጅቱ ለመታደም ሲመጡ በባንኩ ጥበቃዎች የመግቢያ ይለፍ ያገኛሉ፡፡
የሕግ አገልግሎትን የሚያዘምን እና ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ይፋ ሊሆን ነው!
የሕግ ቴክኖሎጂን(LegTech) በመጠቀም በኢትዮጵያ የጥብቅና አገልግሎትን ዘመናዊ ለማድረግ እና ተደራሽነትን ለማስፋት ያለመ ነው::
ኢትዮ ሌጋል ሺልድ ሀላፊነቱ የተወሰነ የጥብቅና ማህበር ከገበያ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ለብዙዎች የሥራ ዕድል የሚፈጥርና ባለሞያውን በቀላሉ ከአገልግሎት ፈላጊው ጋር የሚያገናኝ (AI-powered Legal talent cloud and Matching platform) በቴክኖሎጂ የታገዘ የህግ አገልግሎት ይዞላችሁ ቀርቧል።
ይህ አገልግሎት የህግ ባለሙያዎችንና ደንበኞችን በቀጥታ የሚያገናኝ ከመሆኑ ባሻገር የሕግ አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ የመክፈል አቅም እና የቦታ ርቀት ውስንነት ሳይገደብ ተደራሽ የሚያደርግ በመሆኑ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው።
ይህን ወሳኝ አዲስ ጅምር ለማስተዋወቅ በተዘጋጀው ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀ ግብራችን ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
በዝግጅቱ ላይ፡
• "በቴክኖሎጅ የታገዘ የህግ አገልግሎት በኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ፣ የህግ ቴክኖሎጂ ለፍትህ ተደራሽነትና ለዘርፉ እድገት ስላለው አስተዋጽኦ የሚመክር የፓናል ውይይት ይካሄዳል።
• ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሕግ ግንዛቤ ማስጨበጫ እና የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ለማገልገል የተዘጋጀውን ልዩ የህግ አገልግሎት ለተሳታፊዎች እናስተዋውቃለን።
• የህግ ባለሙያዎች፣ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች፣ የመንግስት ባለድርሻ አካላትና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዚህ ዝግጅት ላይ ተገኝተው ስለህግና ቴክኖሎጂ የወደፊት ሁኔታ ይወያያሉ።
የዝግጅቱ ዝርዝር
• 📅 : ማክሰኞ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
• 🕙: ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ቀኑ 6፡00
• 📍: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት፣ 5ኛ ፎቅ፣ አዲስ አበባ
ለመሳተፍ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ በመጫን ፤መረጃዎን የተሳታፊዎች ዝርዝር ወስጥ በማስመዝገብ ወደ ዝግጅቱ ለመታደም ሲመጡ በባንኩ ጥበቃዎች የመግቢያ ይለፍ ያገኛሉ፡፡
9 months ago