ቴሌቪዥን ግብር ቅሬታ አስነሳ
ነዋሪዎች ከመብራት ክፍያ ጋር እየከፈሉለት ለሚገኘው የቴሌቪዥን አገልግሎት ድጋሚ ክፍያ እየተጠየቅን ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ "ቤት ለቤት እየዞሩ ክፍያ አስገድደውናል" እና "ያለፉት ዓመታት ያልተከፈለ ውዝፍ ክፍያ እንድትከፍሉ ተብለን ደብዳቤ እየተሰጠን ነው" ሲሉ ለGazette Plus ገልጸዋል።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ አስማማው በሪሁ፣ በየወሩ እየከፈሉበት ላለው አንድ ቴሌቪዥን ተጨማሪ ክፍያ እየተጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የተዘበራረቀ አሰራር እንዳለው ይጠቁማሉ።
በተቃራኒው፣ የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላልኝ መለሰ በሰጡት ምላሽ፣ ቤት ለቤት የሚሰበሰበው ክፍያ በአንድ ቤት ውስጥ ለተጨማሪ ቴሌቪዥን ወይም ለንግድ ተቋማት ብቻ መሆኑን ገልጸው፣ በአዋጅ ቁጥር 1278/2015 መሰረት ለእያንዳንዱ መኖሪያ ቤት ለሚገኝ አንድ ቴሌቪዥን ክፍያ ከመብራት ጋር እንደሚከፈል ተናግረዋል።
ሆቴሎች እና ሌሎች የንግድ ተቋማትም ከአንድ በላይ ቴሌቪዥን ካላቸው፣ በቀጣይ ከንግድ ፈቃድ እድሳት ጋር ተያይዞ ክፍያ እንዲፈጽሙ ይደረጋል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ነዋሪዎች ከመብራት ክፍያ ጋር እየከፈሉለት ለሚገኘው የቴሌቪዥን አገልግሎት ድጋሚ ክፍያ እየተጠየቅን ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ "ቤት ለቤት እየዞሩ ክፍያ አስገድደውናል" እና "ያለፉት ዓመታት ያልተከፈለ ውዝፍ ክፍያ እንድትከፍሉ ተብለን ደብዳቤ እየተሰጠን ነው" ሲሉ ለGazette Plus ገልጸዋል።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ አስማማው በሪሁ፣ በየወሩ እየከፈሉበት ላለው አንድ ቴሌቪዥን ተጨማሪ ክፍያ እየተጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የተዘበራረቀ አሰራር እንዳለው ይጠቁማሉ።
በተቃራኒው፣ የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላልኝ መለሰ በሰጡት ምላሽ፣ ቤት ለቤት የሚሰበሰበው ክፍያ በአንድ ቤት ውስጥ ለተጨማሪ ቴሌቪዥን ወይም ለንግድ ተቋማት ብቻ መሆኑን ገልጸው፣ በአዋጅ ቁጥር 1278/2015 መሰረት ለእያንዳንዱ መኖሪያ ቤት ለሚገኝ አንድ ቴሌቪዥን ክፍያ ከመብራት ጋር እንደሚከፈል ተናግረዋል።
ሆቴሎች እና ሌሎች የንግድ ተቋማትም ከአንድ በላይ ቴሌቪዥን ካላቸው፣ በቀጣይ ከንግድ ፈቃድ እድሳት ጋር ተያይዞ ክፍያ እንዲፈጽሙ ይደረጋል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 months ago