Logo
SeledaPost
#ministryofhealth

የብቃት ምዘና ፈተና የሚወስዱ የጤና ባለሙያዎች የኦንላይን ምዝገባ ከሐምሌ 15 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚከናወን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።

አመልካቾች በኦንላይን ሲስተሙ ለመመዝገብ ኮምፒውተር መጠቀም እንደሚኖርባቸው ተመላክቷል። በሞባይል ስልክ ለመመዝገብ መሞከር ምዝገባውን ያልተሟላ ሊያደርገው ይችላል ተብሏል።

ተመዛኞች መደበኛ የEmail አድራሻም ሊኖራችሁ እንደሚገባ ተገልጿል።

ተመዛኞች የብቃት ምዘና ፈተናውን መውሰድ የሚፈልጉበትን የፈተና ጣቢያ ከተዘረዘሩት አማራጮች ውስጥ መምረጥ እንዳለባቸው ፤ እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድሞ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ።

ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ተመዛኞች ምዝገባቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሲስተሙ የሚሰጣቸውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration ID) ፕሪንት አድርገር መያዝ አለባቸው።

ምዝገባቸውን ጀምረው ሳይጨርሱ ያቋረጡ አመልካቾች ዋናው ገጽ ላይ System Login የሚለውን ሊንክ በመጫን Email እና Password አስገብተው ምዝገባቸውን ማጠናቀቅ ይኖርባችኋል ተብሏል።

http://hple.moh.gov.et/hpl... ላይ በመግባትና Registration የሚለውን በመጫን ዝርዝር የፈተናውን መመሪያ ይመልከቱ/ከላይ ያንብቡ።

ይመዝገቡ : http://hple.moh.gov.et/hpl...

Seledadotio
Seledadotio
11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.