Logo
FastMereja
የመብራት ፖል ከገጩ አሽከርካሪዎች ካሳ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ።
#fastmereja I ከተቋቋመ ሁለት አመት ያልሞላው የአዲስ አበባ የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን የከተማዋን መብራት ለማዘመን እየሰራ እንደሚገኝ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሰብስብ ሁሴን (ዶ/ር ) ገልጸዋል ።

በ2018 በጀት አመት በአዲስ አበባ የሚገኙ 41 ሺህ 283 የመብራት ምሰሶዎች መረጃ በጂኦግራፊያዊ መረጃ ስርዓት (GIS ) እንዲደራጁ መደረጉን አስረድተዋል ።

ይህም የከተማዋ የመብራት ምሰሶዎች በዲጂታል የመረጃ ስርዓት ከመያዝ ባለፈ ዘመናዊ በሆነ መልኩ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የመብራት ጥገና ለማከናወን ቁልፍ ስራ መሆኑን ተናግረዋል ።

በበጀት አመቱ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመብራት ምሰሶዎችን ጥንቃቄ በጎደለው ማሽከርከር ከገጩ የካሳ ክፍያ 9 ነጥብ 05 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል ።

18 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.