Logo
Getu Temesgen
የዋሊያዎቹ እና የንግድ ባንኩ ኮከብ አዲስ ግደይ ትዳር መሰረተ!
#ethiopia | ​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እግር ኳስ ክለብ የመስመር አጥቂና የወቅቱ አምበል አዲስ ግደይ በቤተክርስቲያን ሥርዓተ ተክሊል የጋብቻ ሥነ-ሥርዓቱን በደመቀ ሁኔታ ፈጽሟ።

ቀደም ሲል በስልጤ ወራቤ ባሳየው አስደናቂ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ በመሳብ ከስፖርት ቤተሰቡ ጋር የተዋወቀው ይህ ተጫዋች ለሲዳማ ቡና እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦች ጭምር በታማኝነት ማገልገሉ ይታወሳል።

ዛሬ ደግሞ ሕይወቱን ይበልጥ ወደተሟላ ምዕራፍ በማሸጋገር ከረጅም ጊዜ የሕይወት ጓደኛው ጋር የቃል ኪዳን ጋብቻውን በይፋ ፈጽሟል።

ለኮከቡ ተጫዋች አዲስ ግደይ እና ለውድ ባለቤቱ ደስ የሚልና የሰመረ የትዳር ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

credit : balageru tv

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

24 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.