Logo
Getu Temesgen
ወልዋሎ ዓ/ዩ የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ
#eghiopia | አዲስ አበባ – ወልዋሎ ዓ/ዩ በ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ሲዳማ ቡናን 2ለ0 በማሸነፍ የውድድሩ ቻምፒዮን ሆኗል።

ዛሬ ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ፣ ወልዋሎ ዓ/ዩ በኮንኮኒ ሀፊዝ እና በየነ ባንጃ ያስቆጠሯቸው ግቦች ሲዳማ ቡናን 2ለ0 በማሸነፍ የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫን አንስቷል።

ሲዳማ ቡና የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ፣ ወልዋሎ ዓ/ዩ የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ መድረሱን ተከትሎ ኢትዮጵያን በቀጣዩ የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውድድር እንደሚወክል አስቀድሞ ተረጋግጦ ነበር።

የዋንጫ ድሉም ለቡድኑ ታሪካዊ ስኬት ሆኖ ተመዝግቧል።
#ethiopia #ethiopiancup #wolwalo #sidamabunna #cafconfederationcup #getu

27 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.