የኢትዮጵያ መድኃኒት የማምረት አቅም 45 በመቶ ደረሰ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መድኃኒት የማምረት አቅም ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 45 በመቶ ማደጉን አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
በዘርፉ የተመዘገበው ለውጥ የመድኃኒት ጥራት ቁጥጥር ሥርዓቱን በማሻሻሉ የመጣ ውጤት እንደሆነ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ደረጃን በማሟላት ከአፍሪካ ሦስተኛ ደረጃ መያዟ ተነግሯል። ይህ ዕድገት በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶች ለውጭ ገበያ የመቅረብ ዕድላቸውን ከፍ አድርጓል ተብሏል።
የተሻሻለው የቁጥጥር ሥርዓት የማምረት አቅሙን በማሳደግ የኤክስፖርት ተወዳዳሪነትን እያረጋገጠ ነው።
መንግሥት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለሕክምና መሣሪያዎች ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉም ተጠቅሷል።
አሁን ላይ አብዛኛው የሕክምና መሣሪያ ከውጭ አገር በግዢ እንደሚገባ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ በቀጣይ 5 ዓመታት ዘመናዊ የሕክምና ተቋማትን በመገንባት የማምረት አቅሙን የበለጠ ለማሳደግ ታቅዷል ብለዋል።
አሐዱ ሬዲዮ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መድኃኒት የማምረት አቅም ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 45 በመቶ ማደጉን አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
በዘርፉ የተመዘገበው ለውጥ የመድኃኒት ጥራት ቁጥጥር ሥርዓቱን በማሻሻሉ የመጣ ውጤት እንደሆነ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ደረጃን በማሟላት ከአፍሪካ ሦስተኛ ደረጃ መያዟ ተነግሯል። ይህ ዕድገት በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶች ለውጭ ገበያ የመቅረብ ዕድላቸውን ከፍ አድርጓል ተብሏል።
የተሻሻለው የቁጥጥር ሥርዓት የማምረት አቅሙን በማሳደግ የኤክስፖርት ተወዳዳሪነትን እያረጋገጠ ነው።
መንግሥት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለሕክምና መሣሪያዎች ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉም ተጠቅሷል።
አሁን ላይ አብዛኛው የሕክምና መሣሪያ ከውጭ አገር በግዢ እንደሚገባ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ በቀጣይ 5 ዓመታት ዘመናዊ የሕክምና ተቋማትን በመገንባት የማምረት አቅሙን የበለጠ ለማሳደግ ታቅዷል ብለዋል።
አሐዱ ሬዲዮ
29 days ago