Logo
YenetaTube
ታላቁ ምሽት በይፋ ተጀምሯል! ስካይላይት ሆቴል አሁን በደመቀ ሁኔታ ላይ ይገኛል!

ኮካ ኮላ (Coca-Cola) ከዓለም ዋንጫ ጋር ያለውን ታሪካዊ የ50 ዓመታት አጋርነት እና የዘንድሮውን 23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ መጀመር ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ልዩ የመክፈቻ ፕሮግራም አሁን በይፋ ተጀምሯል።

በስካይላይት ሆቴል በተሰናዳው በዚህ እጅግ ማራኪ መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በአንድ ላይ ተሰብስበው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ፣ የፈጠራ እና የመዝናኛ መሰናዶዎች እያደመቁት ይገኛሉ። የዓለም ዋንጫን ታላቅ ስሜት እና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ እያደረስን እንቆያለን!

8 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.