Logo
Getu Temesgen
የጋዜጠኞች እና የቲክቶከሮች ቡድን ለዋንጫ ፍፃሜ ማለፋቸውን አረጋገጡ
#ethiopia | በተደረገው የግማሽ ፍፃሜ የእግር ኳስ ግጥሚያ የጋዜጠኞች ቡድን አርቲስቶችን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ ለዋንጫ ማለፉን አረጋግጧል።

በዚህ ጨዋታ ሙባረክ ፋንታው ድንቅ ብቃቱን በማሳየት የዕለቱ ኮከብ ተጫዋች መሆን ችሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ የቲክቶከሮች ቡድን የድምፃውያንን ቡድን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

በዚህ ጨዋታ ያኪ ለቲክቶከሮች ቡድን ባሳየው እጅግ አዝናኝ እና የተሳካ እንቅስቃሴ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል።

በመሆኑም በመጪው እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት በሚገኘው የኤፍቢኢ ሜዳ የጋዜጠኞች ቡድን ከቲክቶከሮች ጋር ለዋንጫ የሚያደርጉት ታላቅ ፍልሚያ ይጠበቃል።
#የስፖርትዜና #እግርኳስ #ቲክቶክ #ጋዜጠኞች #አዲስአበባ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.