Logo
FIDEL POST NEWS
መካከለኛው ምስራቅ ወደለየለት ጦርነት? ኢራን ከፍተኛ ባለስልጣኖቿ መገደላቸውን አረጋገጠች!

​ኢራን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊዋ አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አረጋገጠች።

ላሪጃኒ የፓርላማ አፈ-ጉባኤ እና የሀገሪቱ የበላይ መሪ አማካሪ የነበሩ ሲሆን፣ በኢራን የፖለቲካ እና የደህንነት መዋቅር ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ግለሰብ ናቸው።

​በተጨማሪም የባሲጅ ጦር አዛዥ ጎላምሬዛ ሶለይማኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ የኢራን አብዮት ጥበቃ ጦር ጠንካራ የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ ዝቷል።

​በሌላ በኩል፦
​አሜሪካ፦ ለእስራኤል ሙሉ ድጋፏን በመግለጽ ጥቃቱ እንዲቀጥል አሳስባለች።

​ኢራን፦ አሜሪካ እግረኛ ጦር የምትልክ ከሆነ "አዲስ ቬትናም" ይጠብቃታል ስትል አስጠንቅቃለች።

​ውጥረት፦ ቴህራን ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ሚሳኤሎችን በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ መተኮሷ ተዘግቧል።
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.