5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት በአዲስ አበባ በይፋ ተከፈተ!
#fastmereja I “ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት” በሚል መሪ ቃል፣ 5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዛሬ በየካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተከፍቷል።
ከ120 በላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን ለህዝብ በኤግዚቢሽን የሚያቀርቡበት ሲሆን፣ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
በቆይታው በስምንት አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ከነዚህም መካከል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና በጠቅላላ ምርጫ፣ በሰላም ግንባታ፣ በስርዓተ ጾታ እና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ይገኙበታል።
በመድረኩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።
ይህ መድረክ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና ከህዝብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
#ኹነት
#fastmereja I “ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት” በሚል መሪ ቃል፣ 5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዛሬ በየካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተከፍቷል።
ከ120 በላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን ለህዝብ በኤግዚቢሽን የሚያቀርቡበት ሲሆን፣ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
በቆይታው በስምንት አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ከነዚህም መካከል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና በጠቅላላ ምርጫ፣ በሰላም ግንባታ፣ በስርዓተ ጾታ እና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ይገኙበታል።
በመድረኩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።
ይህ መድረክ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና ከህዝብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
#ኹነት
5 months ago