Logo
YenetaTube
ኢራን የመሪዋን አያቶላ አሊ ኻሜኒን ሞት አረጋገጠች
የኔታ ሚዲያ

የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ የሀገሪቱ ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል ጥምር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አስታወቀ።

ዜናውን ያበሰረው ጋዜጠኛ ጥልቅ በሆነ ሐዘን እና በእንባ ታጅቦ በፋርሲ ቋንቋ ያነበበው ይፋዊ መግለጫ የሚከተለውን ይላል፦
"ያለ እረፍት እና ድካም ለዘለቀው የሁሴኒ ተጋድሎ ሕይወት በኋላ እንደ እስላማዊ ጥበቃ ጽኑ ተራራ በሆነው ታላቅ እና ሰማያዊ መንፈስ፤ የርኅራኄ እና የቁርጠኝነት አባት፣ የሙስሊሞች መሪ እና ኢማም፣ ክቡር አያቶላ ሰይድ አሊ ሁሴኒ ኻሜኒ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክን ቅዱስ መቅደስ ክብር የማስጠበቅ ጉዞ ላይ ሳሉ ጣፋጩን የሰማዕትነት ጽዋ በመጎንጨት ወደ ልዑል ሰማያዊው መንግሥት ተቀላቅለዋል።"
እንደ ዘገባው ከሆነ መሪው ለህልፈት የተዳረጉት በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል የተሰነዘሩ ጥቃቶችን ተከትሎ ነው።

በቴህራን እና በሌሎች ዋና ዋና ከተሞች ከፍተኛ የሐዘን ድባብ እየታየ ነው

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.