አይሾው ስፒድ (IShowSpeed) የጋና ፓስፖርት ሊሰጠው ነው
#fastmereja I ታዋቂው አሜሪካዊ የኢንተርኔት ሰው Darren Watkins Jr. (በተለዋጭ ስሙ አይሾው ስፒድ) በቅርቡ በጋና ባደረገው ጉብኝት ወቅት እናቱ ጋናዊት መሆኗን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ መንግስት የጋና ፓስፖርት እንዲሰጠው ወስኗል።
ስፒድ በጋና በነበረው ቆይታ እናቱ የጋና ተወላጅ መሆኗን ለተከታዮቹ ገልጿል። ይህም "ወደ ቤቴ ተመልሻለሁ" በማለት ደስታውን እንዲገልጽ አድርጎታል።
የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ሳሙኤል ኦኩዴቶ አብላክዋ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስፒድ ለጋና በጎ ገጽታን በመገንባት ረገድ ያሳየው ተነሳሽነት የሚደነቅ በመሆኑ የጋና ፓስፖርት እንዲሰጠው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው ማጽደቁን አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ስፒድን ለጋና "ተገቢ አምባሳደር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ በዲጂታል ሚዲያ ያለውን ግዙፍ ተፅዕኖ ለሀገሪቱ ገጽታ ግንባታ እንደሚጠቅም ገልጸዋል።
ስፒድ ይህንን ውሳኔ ያገኘው ኢትዮጵያን ጨምሮ 20 የአፍሪካ ሀገራትን ለ28 ቀናት በጎበኘበት "Speed Does Africa" በተሰኘው ታሪካዊ ጉዞው ማጠቃለያ ላይ ነው።
ይህ እርምጃ ጋና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ትውልደ ጋናውያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የምታደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ተወስዷል። ስፒድ በአሁኑ ወቅት በዩቲዩብ (YouTube) ብቻ ከ50 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ሲሆን፣ የአፍሪካ ጉዞው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ ነበር።
#fastmereja I ታዋቂው አሜሪካዊ የኢንተርኔት ሰው Darren Watkins Jr. (በተለዋጭ ስሙ አይሾው ስፒድ) በቅርቡ በጋና ባደረገው ጉብኝት ወቅት እናቱ ጋናዊት መሆኗን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ መንግስት የጋና ፓስፖርት እንዲሰጠው ወስኗል።
ስፒድ በጋና በነበረው ቆይታ እናቱ የጋና ተወላጅ መሆኗን ለተከታዮቹ ገልጿል። ይህም "ወደ ቤቴ ተመልሻለሁ" በማለት ደስታውን እንዲገልጽ አድርጎታል።
የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ሳሙኤል ኦኩዴቶ አብላክዋ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስፒድ ለጋና በጎ ገጽታን በመገንባት ረገድ ያሳየው ተነሳሽነት የሚደነቅ በመሆኑ የጋና ፓስፖርት እንዲሰጠው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው ማጽደቁን አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ስፒድን ለጋና "ተገቢ አምባሳደር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ በዲጂታል ሚዲያ ያለውን ግዙፍ ተፅዕኖ ለሀገሪቱ ገጽታ ግንባታ እንደሚጠቅም ገልጸዋል።
ስፒድ ይህንን ውሳኔ ያገኘው ኢትዮጵያን ጨምሮ 20 የአፍሪካ ሀገራትን ለ28 ቀናት በጎበኘበት "Speed Does Africa" በተሰኘው ታሪካዊ ጉዞው ማጠቃለያ ላይ ነው።
ይህ እርምጃ ጋና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ትውልደ ጋናውያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የምታደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ተወስዷል። ስፒድ በአሁኑ ወቅት በዩቲዩብ (YouTube) ብቻ ከ50 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ሲሆን፣ የአፍሪካ ጉዞው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ ነበር።
4 months ago