Logo
Getu Temesgen
🇪🇹 ኢትዮጵያዊቷ ሼፍ ለታላቁ የ"ጄምስ ቢርድ" ሽልማት ታጨች! 👩‍🍳🏆

​"የምግብ ዓለም ኦስካር በሆነው መድረክ የኢትዮጵያን ጣዕም አድምቃለች"

​በሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ የሚገኘው የ"ቤተሰብ ሬስቶራንት" (Beteseb Restaurant) ባለቤት እና ሼፍ የሆነችው ዳርምየለሽ ዓለሙ፤ ለ2026 የጄምስ ቢርድ (James Beard Awards) "የሚድ-አትላንቲክ ምርጥ ሼፍ" ዕጩ ተወዳዳሪ (Semifinalist) ሆና ተመርጣለች!
​ይህ ሽልማት በአሜሪካ የምግብ ኢንዱስትሪ ትልቁ እና ክብር የሚሰጠው ሽልማት ነው።

​ለምን ልዩ ይሆናል?
🌟 ከ20 ዕጩዎች መካከል ከሜሪላንድ ስቴት የተመረጡት ሁለት ሲሆኑ፤ ከሞንትጎመሪ ካውንቲ (Montgomery County) ደግሞ ብቸኛዋ ተወዳዳሪ እሷ ነች።

🌟 ቤተሰብ ሬስቶራንት በዋሽንግተንያን (Washingtonian) የ2026 ምርጥ 100 ሬስቶራንቶች ዝርዝር ውስጥ 46ኛ ደረጃን ይዞ ነበር።

🌟 በታዋቂው ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰን የቲቪ ፕሮግራም ላይ በመቅረብ የኢትዮጵያን ምግብ አስተዋውቃለች።

​በውድድሩ አሸናፊ ሆና እንድትወጣ መልካም ምኞታችንን እንግለጽላት!

ዲሲ እና ሜሪላንድ አካባቢ ያላችሁ ጎራ ብላችሁ ሙያዋን አድንቁ!

​📍 አድራሻ:
8201 Georgia Ave, Silver Spring, MD

📅 የፍጻሜ ውጤት: ሰኔ 15 ይገለጻል።

​#ethiopianpride #jamesbeard2026 #chefdarmyelesh #betesebrestaurant #silverspring #ethiopianfood #dmveats #semifinalist

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.