Logo
Getu Temesgen
⚫ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አሜሪካ ውስጥ በድንገት አረፉ

​"ባደሩበት ሆቴል ሞተው ተገኝተዋል!"
#ethiopia | ​ለስራ ጉዳይ ወደ አሜሪካ ተጉዘው የነበሩት የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የፊዚክስ ምሁሩ ዶ/ር ለታ ተስፋዬ፤ በትናንትናው ዕለት ባደሩበት ሆቴል ውስጥ ህይወታቸው አልፎ መገኘቱ ተሰማ።

​ዩኒቨርሲቲው በሰጠው መግለጫ፤ ዶ/ር ለታ ለ6 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት ባገለገሉበት ወቅት "ትውልድን ማብቃት" በሚል መርህ በትጋት የሰሩ እና በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ መሪ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ አሟሟታቸውን "ያልተጠበቀ ህይወተ እልፈት" ሲል ገልጾታል።

​ዶ/ር ለታ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር እና በፊዚክስ ዘርፍ ትልቅ አሻራ ያሳረፉ ውድ የሀገር ልጅ ነበሩ።
​ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሙያ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።

​ነፍስ ይማር! 🕯️

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

​#drletatesfaye #dembidolouniversity #restinpeace #ethiopia #education

7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.