Logo
Getu Temesgen
እጅ ከፍንጅ! ጉቦ ሲቀበል የነበረው የኦዲት ባለሙያ በቁጥጥር ስር ዋለ
#ethiopia | ​"ሰነድህ ትክክል አይደለም" እያሉ የግብር ከፋዩን መብት በመርገጥ ጉቦ የጠየቁ አካላት በሕግ ወጥመድ ገብተዋል።

​በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የቦሌ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኦዲት ባለሙያ እና አስተባባሪ፤ አንድ ግብር ከፋይ ያቀረበውን የ3 ሚሊዮን ብር ሕጋዊ የወጪ ሰነድ "አንቀበልም" በማለት ለአንድ ወር ሲያመላልሱት ቆይተዋል።

​ነገሩ ወዲህ ነው...
እነዚህ አካላት ትክክለኛውን ሰነድ ወደ ጎን በመተው ጉቦ እንዲሰጣቸው ግብር ከፋዩን ወጥረው ይይዛሉ። ግብር ከፋዩ ግን በድርጊቱ ባለመተባበር በቢሮው 7075 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ ይሰጣሉ።

​በተደረገው ክትትልም፦
ባለሙያው 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር ጉቦ ሲቀበል ፖሊስ እጅ ከፍንጅ ይዞታል። የኦዲት አስተባባሪዋም ከኃላፊነት ተነስተው ጉዳዩ እየተመረመረ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ​መልዕክት:
ሌብነትን ዝም አንበል! ግብር ከፋዩ እንዳደረገው በ 7075 በመደወል የበኩላችንን እንወጣ።

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

​#addisababa #revenuesbureau #anticorruption #7075 #justice #bole

5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.